Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 17 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰውን ከም​ድር ፈጠ​ረው፥ ዳግ​መ​ኛም ወደ ምድር ይመ​ል​ሰ​ዋል።

2 ዓመ​ታ​ት​ንና ቀና​ትን በቍ​ጥር ሰጣ​ቸው፤ በው​ስ​ጧም ያለ​ውን ሁሉ አስ​ገ​ዛ​ቸው።

3 ለእ​የ​ራ​ሳ​ቸው ኀይ​ልን አሳ​ደ​ረ​ባ​ቸው፤ በም​ሳ​ሌ​ውም ፈጠ​ራ​ቸው።

4 ፍጥ​ረቱ ሁሉ እን​ዲ​ፈ​ሩ​አ​ቸው አደ​ረገ።

5 አው​ሬ​ዎ​ች​ንና ወፎ​ች​ንም እን​ዲ​ገ​ዟ​ቸው አደ​ረገ።

6 ቃል​ንና አን​ደ​በ​ትን፥ ዐይ​ንና ጆሮን፥ የሚ​ያ​ስ​ቡ​በት ልቡ​ና​ንም ሰጣ​ቸው።

7 ጥበ​ብን ማወ​ቅ​ንም አጠ​ገ​ባ​ቸው፤ ክፉ​ንና በጎ​ንም አሳ​ያ​ቸው።

8 የሥ​ራ​ውን ገና​ና​ነ​ትና መፈ​ራ​ቱ​ንም ያሳ​ያ​ቸው ዘንድ፥ በል​ቡ​ና​ቸው ፍር​ሀ​ትን አሳ​ደ​ረ​ባ​ቸው።

9 ቅዱስ ስሙን ያመ​ሰ​ግ​ኑት ዘንድ።

10 የሥ​ራ​ው​ንም ገና​ና​ነት ይና​ገሩ ዘንድ፥

11 ጥበ​ብን ሰጣ​ቸው፤ የሚ​ያ​ድ​ና​ቸው ሕጉ​ንም አወ​ረ​ሳ​ቸው።

12 የዘ​ለ​ዓ​ለም መሐ​ላ​ንም ተማ​ማ​ላ​ቸው፤ ፍር​ዱ​ንም ነገ​ራ​ቸው።

13 ዐይ​ኖ​ቻ​ቸ​ውም የጌ​ት​ነ​ቱን ገና​ና​ነት አዩ።

14 የጌ​ት​ነ​ቱ​ንም ቃል ጆሮ​ቻ​ቸው ሰሙ፥

15 ከኀ​ጢ​አት ሁሉ ተጠ​በቁ አላ​ቸው፤ ሁሉ​ንም ባል​ጀ​ራ​ች​ሁን ውደዱ ብሎ አዘ​ዛ​ቸው።

16 መን​ገ​ዳ​ቸ​ውም ሁል​ጊዜ በፊቱ ነው፥ ከዐ​ይ​ኖ​ቹም የሚ​ሰ​ወ​ሩ​በት የላ​ቸ​ውም።

17 ለአ​ሕ​ዛብ ሁሉ ነገ​ሥ​ታ​ትን አነ​ገ​ሠ​ላ​ቸው።

18 እስ​ራ​ኤል ግን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክፍል ሆነ።

19 ሥራ​ቸ​ውም ሁሉ በፊቱ እንደ ፀሐይ ነው፤ ዐይ​ኖ​ቹም ሁል​ጊዜ መን​ገ​ዳ​ቸ​ውን ያያሉ።

20 ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውም ከእ​ርሱ አል​ተ​ሰ​ወ​ረ​ችም፤ በደ​ላ​ቸ​ውም ሁሉ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ነው።

21 የሰው ምጽ​ዋቱ ከእ​ርሱ ጋራ እንደ ማኅ​ተም ነው።

22 የሰው ዋጋው እንደ ዐይን ብሌን ትጠ​በ​ቅ​ለ​ታ​ለች።

23 ኋላ ተመ​ልሶ ዋጋ​ቸ​ውን ይሰ​ጣ​ቸ​ዋል፤ የኀ​ጢ​አ​ታ​ቸ​ው​ንም ፍዳ ወደ ራሳ​ቸው ይመ​ል​ሳል።

24 ነገር ግን ንስሓ የሚ​ገ​ቡ​በ​ትን መን​ገድ ሰጣ​ቸው፤ ተስፋ የቈ​ረጡ ሰዎ​ች​ንም ደስ ያሰ​ኛ​ቸ​ዋል።


የን​ስሓ ጥሪ

25 ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተመ​ለስ፥ ኀጢ​አ​ት​ንም ተዋት በፊ​ቱም ጸልይ፥ ለበ​ደ​ል​ህም ንስሓ ግባ፤

26 ከበ​ደ​ል​ህም ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተመ​ለስ፤ ኀጢ​አ​ትን ሁሉ ጥላ ፈቃ​ዱ​ንም አድ​ርግ።

27 በሕ​ይ​ወት ሳሉ እን​ደ​ሚ​ገ​ዙ​ለት ሰዎች፥ ልዑ​ልን በመ​ቃ​ብር የሚ​ያ​መ​ሰ​ግ​ነው ማን​ነው?

28 የሞተ ሰውን ግን ንስሓ እንደ ኢም​ንት አለ​ፈው፤ በሕ​ይ​ወ​ትህ ደስ እያ​ለህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግ​ነው።

29 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቸር​ነቱ ታላቅ ነውና፤ የሚ​ገ​ዙ​ለ​ትን ሰዎች ይቅር ይላ​ቸ​ዋል።

30 ሰው ሟች ስለ ሆነ፥ ሁሉ በሰው ዘንድ ሊሆን አይ​ች​ልም።

31 ከፀ​ሐይ የሚ​በራ ምን አለ? እር​ሱም እንኳ ያል​ፋል። ደማ​ዊና ሥጋ​ዊም ክፉ ነገ​ርን ያስ​ባል።

32 እርሱ የሰ​ማ​ይን ምጥ​ቀት ኀይል ያው​ቃል፥ ሰው ሁሉ ግን አመ​ድና ትቢያ ነው።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች