Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 16 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ጥቅም የሌ​ላ​ቸው ብዙ ልጆ​ችን አት​መኝ፤ በክ​ፉ​ዎች ልጆ​ችም ደስ አይ​በ​ልህ።

2 በእ​ነ​ርሱ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት ከሌ​ለ​ባ​ቸው፥ ቢበ​ዙም በእ​ነ​ርሱ ደስ አይ​በ​ልህ።

3 በሕ​ይ​ወ​ታ​ቸ​ውም አት​ተ​ማ​መ​ን​ባ​ቸው፥ ብዛ​ታ​ቸ​ውም ደስ አያ​ሰ​ኝህ። ከሺህ አንድ ደግ ይሻ​ላል፥ ክፉን ከመ​ው​ለ​ድም ሳይ​ወ​ልዱ መሞት ይሻ​ላል።

4 በአ​ንድ ዐዋቂ ሀገር ትጸ​ና​ለ​ችና፥ በኀ​ጢ​አ​ተ​ኞች ብዛት ግን ትጠ​ፋ​ለች።

5 ዐይኔ እን​ዲህ ያለ ብዙ ነገ​ርን አየች። ጆሮ​ዬም ከዚህ የሚ​በ​ልጥ ሰማች።

6 በኀ​ጢ​አ​ተ​ኞች ወገ​ኖች እሳት ትነ​ድ​ዳ​ለች፤ በወ​ን​ጀ​ለ​ኞች ሕዝብ ላይም ጥፋት ትነ​ድ​ዳ​ለች።

7 በኀ​ይ​ላ​ቸው የታ​መኑ የቀ​ደሙ አር​በ​ኞ​ችም ራሳ​ቸ​ውን አላ​ዳ​ኑም።

8 ሎጥ ለኖ​ረ​ባ​ቸው፥ ራሳ​ቸ​ው​ንም ላኮሩ፥ ሎጥ​ንም ለተ​ጸ​የ​ፉት ሀገ​ሮች አል​ራ​ራ​ላ​ቸ​ውም።

9 ኀጢ​አ​ተ​ኞች ሕዝ​ቦ​ችን ይቅር አላ​ላ​ቸ​ውም፤ በኀ​ጢ​አ​ታ​ቸው ጠፉ እንጂ።

10 እነ​ዚ​ህም የተ​ሰ​በ​ሰቡ፥ ልቡ​ና​ቸ​ው​ንም ያከፉ፥ ስድ​ስት መቶ ሺህ እግ​ረ​ኞች ነበሩ።

11 ክሣደ ልቡ​ና​ውን ያጸና አንድ ሰው ቢኖር እርሱ ቢድን ድንቅ ነው፥ ይቅ​ር​ታም መቅ​ሠ​ፍ​ትም ከእ​ርሱ ዘንድ ነውና ይቅር ማለት ይች​ላል፤ መቅ​ሠ​ፍ​ት​ንም ማም​ጣት ይች​ላል።

12 ቍጣው እንደ ቸር​ነቱ ብዛት መጠን ነው፥ ለሰ​ውም እንደ ሥራው ይከ​ፍ​ለ​ዋል።

13 ኀጢ​አ​ተኛ ሰው ከዳፋ አያ​መ​ል​ጥም፤ ጻድቅ ሰውም የት​ዕ​ግ​ሥ​ቱን ዋጋ አያ​ጣም።

14 ምጽ​ዋት ሁሉ ይቅ​ር​ታን ያመ​ጣል፤ ሰውም ሁሉ እንደ ሥራው ያገ​ኛል።

15 “ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አመ​ል​ጣ​ለሁ፤ በሰ​ማ​ያ​ትም የሚ​ያ​ገ​ኘኝ የለም።

16 በብዙ አሕ​ዛ​ብም ዘንድ የሚ​ያ​ው​ቀኝ የለም።

17 የሰ​ው​ነ​ቴስ ቍጥሯ በዓ​ለም ሁሉ ምን​ድን ነው?” አት​በል።

18 እነሆ፥ ሰማይ፥ ከሰ​ማ​ያ​ትም በላይ ያለ ሰማይ፥ ከሰ​ማ​ይም በታች ያለ ውቅ​ያ​ኖስ፥ ምድ​ርም፥ በመ​ዓት በጐ​በ​ኛ​ቸው ጊዜ ይህ ሁሉ ይነ​ዋ​ወ​ጣል።

19 ተራ​ሮ​ችም፥ የም​ድ​ርም መሠ​ረ​ቶች፥ በመ​ዓት ባያ​ቸው ጊዜ ይን​ቀ​ጠ​ቀ​ጣሉ ይነ​ዋ​ወ​ጣ​ሉም።

20 ይህ​ንም ልብ አያ​ስ​በ​ውም፤ መን​ገ​ዶ​ቹ​ንስ ማወቅ ማን ይች​ላል? ገና​ና​ነ​ቱ​ንስ ጠብቆ መና​ገር ማን ይች​ላል?

21 ከሥ​ራ​ውም አብ​ዛ​ኛው ስውር ነው፥ ሰው የማ​ያ​የው ዐውሎ ነፋስ ነውና።

22 እው​ነት ሥራ መሥ​ራ​ትን ማን ያስ​ተ​ም​ራል? የም​ሕ​ረ​ቱ​ንስ ተስፋ ማን ደጅ ይጠ​ናል?

23 አእ​ምሮ የሌ​ለው ሰው እን​ዲህ ያስ​ባል፤ ሰነ​ፍና በደ​ለኛ ሰውም ስን​ፍ​ናን ያስ​ባል።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጥበብ በሥነ ፍጥ​ረት

24 ልጄ ሆይ፥ ስማኝ፥ ጥበ​ብ​ንም ተማር፥ ነገ​ሬ​ንም ከል​ቡ​ናህ አድ​ም​ጠው።

25 በሚ​ዛን መዝ​ነህ ጥበ​ብ​ህን ግለ​ጣት፤ የት​ም​ህ​ር​ት​ህ​ንም ነገ​ሯን ተረዳ።

26 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሥራ ከጥ​ንት ጀምሮ በሥ​ል​ጣኑ ተፈ​ጠረ። ሥር​ዐ​ታ​ቸ​ው​ንም በየ​ወ​ገ​ና​ቸው ለየ።

27 ዓለም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ጸንቶ ይኖር ዘንድ ሥራ​ውን ሁሉ አዘ​ጋጀ፥ ሠራ​ዊ​ታ​ቸ​ው​ንም በየ​ወ​ገ​ና​ቸው አዘ​ጋጀ፥ አይ​ሠ​ሩም፥ አይ​ጠ​ሙም፥ አይ​ራ​ቡ​ምም፥ ሥራ​ቸ​ውም አይ​ቋ​ረ​ጥም፤

28 አንዱ ከሌ​ላው ጋር አይ​ጨ​ና​ነ​ቅም፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ሙም ከቃሉ አይ​ወ​ጡም።

29 ከዚህ በኋላ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምድ​ርን ተመ​ለ​ከተ፤ ከበ​ረ​ከ​ቱም አጠ​ገ​ባት።

30 በደ​ማ​ዊት ነፍስ ሕያው የሆነ ፍጥ​ረት ሁሉ በም​ድር መላ፤ መመ​ለ​ሻ​ቸ​ውም ወደ ምድር ነው።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች