Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 15 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈራ ሰው እን​ዲህ ያደ​ር​ጋል፤ ሕጉ​ንም የሚ​ጠ​ብቅ ሰው ጥበ​ብን ያገ​ኛ​ታል።

2 እንደ እናቱ ትን​ከ​ባ​ከ​በ​ዋ​ለች፤ እንደ ቆንጆ ሴትም ትቀ​በ​ለ​ዋ​ለች።

3 የጥ​በ​ብን እህል ትመ​ግ​በ​ዋ​ለች፤ የዕ​ው​ቀ​ት​ንም ውኃ ታጠ​ጣ​ዋ​ለች።

4 በእ​ር​ስዋ ይመ​ረ​ኰ​ዛል፥ አይ​ፍ​ገ​መ​ገ​ምም፤ የሚ​ታ​መ​ን​ባ​ትም አያ​ፍ​ርም።

5 ከባ​ል​ን​ጀ​ራው ይልቅ ከፍ ከፍ ታደ​ር​ገ​ዋ​ለች፥ በብዙ ሰዎች መካ​ከ​ልም አፉን ገልጦ ይና​ገ​ራል።

6 ደስ​ታን ትሰ​ጠ​ዋ​ለች፥ የደ​ስታ ዘው​ድ​ንም ታቀ​ዳ​ጀ​ዋ​ለች፥ ስሙ​ንም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ያስ​ጠ​ራል።

7 አላ​ዋ​ቂ​ዎች ግን አያ​ገ​ኙ​አ​ትም፤ ኀጢ​አ​ተ​ኞ​ችም አያ​ዩ​አ​ትም።

8 ከት​ዕ​ቢ​ተ​ኞች ሰዎ​ችም የራ​ቀች ናት፤ ሐሰ​ተ​ኞች ሰዎች አያ​ስ​ቧ​ትም።

9 የኀ​ጢ​አ​ተኛ ሰው የቃሉ ነገር ያማረ አይ​ደ​ለም፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በመ​ፍ​ራት የሚ​ና​ገር አይ​ደ​ለ​ምና።

10 ምሳ​ሌን በጥ​በብ ይና​ገ​ሯ​ታል፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የሚ​ማ​ራ​ትን ሰው ይረ​ዳ​ዋል።

11 “ስለ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ብዬ ተከ​ለ​ከ​ልሁ” አት​በል፤ እርሱ የሚ​ጠ​ላ​ው​ንም አታ​ድ​ርግ።

12 “እርሱ አሳ​ተኝ” አት​በል፤ እር​ሱስ ኀጢ​አ​ተኛ ሰውን አይ​ወ​ድ​ድም፤

13 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የረ​ከ​ሰ​ውን ሁሉ ይጠ​ላ​ልና፤ የሚ​ፈ​ሩ​ት​ንም ሰዎች ይወ​ዳ​ቸ​ዋል።

14 እርሱ አስ​ቀ​ድሞ ሰውን በን​ጽሕ ፈጠ​ረው፥ እንደ ጠባ​ዩም በወ​ደ​ደው እን​ዲ​ሠራ ተወው።

15 ትእ​ዛ​ዙን ትጠ​ብቅ ዘንድ፥ ሃይ​ማ​ኖ​ቱ​ንም ታጸና ዘንድ ብት​ወድ ግን ፈቃዱ ነው።

16 እጅ​ህን በመ​ረ​ጥ​ኸው ትጨ​ምር ዘንድ፥ እነሆ፥ እሳ​ት​ንና ውኃን አኖ​ረ​ልህ።

17 ሕይ​ወ​ትና ሞትም በሰው ፊት ናቸው፥ ከእ​ነ​ር​ሱም የመ​ረ​ጠ​ውን ይሰ​ጡ​ታል።

18 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጥበቡ ታላቅ ነውና፥ ኀይ​ሉም የጸና ነውና ሁሉን ያው​ቃል፥ ሁሉ​ንም ያያል።

19 ዐይ​ኖ​ቹም የሚ​ፈ​ሩ​ትን ሰዎች ይመ​ለ​ከ​ታሉ፤ እር​ሱም የሰ​ውን ሥራ ሁሉ ያው​ቃል።

20 እር​ሱስ ኀጢ​አ​ትን ይሠራ ዘንድ ያዘ​ዘው የለም፤ ይበ​ድ​ልም ዘንድ ማን​ንም አላ​ሰ​ና​በ​ተም፤

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች