Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 13 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ከጓ​ደኛ ስለ መጠ​በቅ

1 አደሮ ማር የዳ​ሰሰ ሰው በእ​ርሱ ይያ​ዛል፤ ትዕ​ቢ​ተኛ ሰው​ንም ወዳጅ ያደ​ረገ እንደ እርሱ ይሆ​ናል።

2 የከ​በደ ሸክ​ምን አን​ሥ​ተህ በራ​ስህ አት​ሸ​ከም፥ ገን​ዘ​ብ​ህ​ንም ከሚ​በ​ረ​ታ​ብ​ህና ከባ​ለ​ጸጋ ገን​ዘብ ጋራ አት​ጨ​ምር፥ የሸ​ክላ ድስት ከብ​ረት ድስት ጋር በየት አንድ ይሆ​ናል? እር​ስዋ መትታ እር​ስዋ ትጮ​ኻ​ለ​ችና፥ እር​ስ​ዋም ትሰ​ብ​ራ​ለ​ችና።

3 እን​ደ​ዚሁ ሁሉ ባለ ጸጋ እርሱ ይበ​ድ​ላል፥ እር​ሱም ይቈ​ጣል፤ ድሃ ግን እርሱ ይገ​ፋል፥ እር​ሱም ይለ​ማ​መ​ጣል።

4 የም​ት​ጠ​ቅ​መው ነገር ቢኖር ወደ እርሱ ያቀ​ር​ብ​ሃል፤ ብት​ቸ​ገር ግን ከዚያ በኋላ አያ​ይ​ህም።

5 ገን​ዘብ ቢኖ​ርህ ከአ​ንተ ጋራ አንድ ይሆ​ናል፥ ያን​ተ​ንም ይጨ​ር​ስ​ል​ሃል፤ ዳግ​መ​ኛም አያ​መ​ሰ​ግ​ን​ህም።

6 አን​ተን የሚ​ፈ​ል​ግ​በት ግዳጅ ቢኖ​ረው ያባ​ብ​ል​ሃል፤ ብዙ ተስ​ፋም ይሰ​ጥ​ሃል፤ ይሥ​ቅ​ል​ሃል፤ በጎ ነገ​ርም ይና​ገ​ር​ሃል፤ ምን ትፈ​ል​ጋ​ለ​ህም ይል​ሃል።

7 በመ​ብ​ሉም ይሸ​ነ​ግ​ል​ሃል፤ አንድ ጊዜ፥ ሁለት ጊዜ፥ ሦስት ጊዜም ያስ​ት​ሃል፤ ከዚ​ህም በኋላ እን​ደ​ማ​ይ​ሰ​ማህ ወደ ኋላ ይመ​ለ​ሳል፤ ቢያ​ይ​ህም ይሥ​ቅ​ብ​ሃል፤ ራሱ​ንም ይነ​ቀ​ን​ቅ​ብ​ሃል።

8 እን​ዳ​ያ​ስ​ት​ህና እን​ዳ​ያ​ታ​ል​ልህ ከእ​ን​ዲህ ያለ ሰው ተጠ​በቅ፥ በደ​ስ​ታ​ህም መካ​ከል ኀዘን አታ​ግባ።

9 ባለ​ጸጋ ያዘ​ዘ​ህን ለጊ​ዜው እሽ በለው፥ ቢጠ​ራ​ህም እንቢ አት​በ​ለው፤ ፈጽ​ሞም ይወ​ድ​ሃል።

10 አት​ራቅ አት​ሳ​ትም፥ ነገር ግን እን​ዳ​ይ​ዘ​ነ​ጋህ ፈጽ​መህ አት​ራ​ቀው።

11 ከእ​ርሱ ጋር ነገ​ርን አታ​ብዛ፤ በነ​ገሩ ብዛት ይፈ​ት​ን​ሃ​ልና፤ ከአ​ን​ተም ጋራ የሚ​ሥቅ መስሎ ይመ​ረ​ም​ር​ሃ​ልና በነ​ገሩ ብዛት አት​መ​ነው።

12 መታ​ሰ​ሩና ጥፋቱ አያ​ሳ​ዝ​ነ​ው​ምና፥ የባ​ል​ን​ጀ​ራ​ውን ምሥ​ጢር ለሚ​ያ​ወጣ ሰው ይቅ​ርታ የለ​ውም።

13 ከገ​ዳ​ይህ ጋር ትሄ​ዳ​ለ​ህና ዕወቅ፤ አጥ​ብ​ቀ​ህም ተጠ​በቅ።

14 ከብት ሁሉ ዘመ​ዱን ይወ​ድ​ዳል፤ ሰውም ሁሉ ባል​ን​ጀ​ራ​ውን ይወ​ድ​ዳል።

15 ፍጥ​ረቱ ሁሉ እንደ እርሱ ካለ ፍጥ​ረት ጋራ አንድ ይሆ​ናል፤ ሰውም የሚ​መ​ስ​ለ​ውን ይከ​ተ​ላል።

16 ተኵላ ከበግ ጋር በየት ወዳጅ ይሆ​ናል? ኀጢ​አ​ተኛ ሰውም ከጻ​ድቅ ሰው ጋራ እን​ዲሁ ነው።

17 ውሾ​ችን ከጅ​ቦች ጋር ማን ያስ​ማ​ማ​ቸ​ዋል? ድሃ​ው​ንስ ከባ​ለ​ጸ​ጋው ጋራ ማን ወዳጅ ያደ​ር​ገ​ዋል?

18 የሜዳ አህ​ዮች የአ​ን​በ​ሶች አደን ናቸው፤ እን​ደ​ዚ​ሁም ሁሉ ባለ​ጸ​ጋው ድሃ​ውን ይቀ​ማ​ዋል።

19 ትዕ​ቢ​ተኛ ሰው ራሱን የሚ​ያ​ዋ​ር​ደ​ውን ሰው ይጸ​የ​ፈ​ዋል፤ እን​ዲ​ሁም ሁሉ ባለ​ጸ​ጋው ድሃ​ውን ይጸ​የ​ፈ​ዋል።

20 ባለ​ጸጋ ቢፍ​ገ​መ​ገም ወዳ​ጆቹ ይደ​ግ​ፉ​ታል፤ ድሃ ግን ቢወ​ድቅ ባል​ን​ጀ​ሮቹ ይረ​ግ​ጡ​ታል።

21 ባለ​ጸጋ ቢያ​ድ​ጠው ብዙ ሰዎች ያነ​ሡ​ታል፥ ክፉ ቢና​ገ​ርም ነገ​ሩን ያቀ​ኑ​ለ​ታል፤ ድሃ ግን ቢስት ይረ​ግ​ሙ​ታል፤ በጎ ነገ​ርም ቢና​ገር አያ​ደ​ም​ጡ​ትም።

22 ባለ​ጸጋ ቢና​ገር ሁሉ ዝም ይላል፤ ቃሉ​ንም ያደ​ን​ቁ​ለ​ታል፥ ነገ​ሩ​ንም እስከ ደመና ያደ​ር​ሱ​ለ​ታል፤ ድሃ ግን ምንም በጎ ነገር ቢና​ገር ይህ ምን​ድን ነው? ይሉ​ታል፤ ቢሰ​ነ​ካ​ከ​ልም ያዳ​ፉ​ታል።

23 ኀጢ​አት ሳት​ሠራ ባለ​ጸ​ግ​ነት መል​ካም ነው፤ ኃጥእ ድህ​ነ​ቱን ባፉ ያክ​ፋ​ፋ​ታል።

24 ደስ ቢለው፥ ቢያ​ዝ​ንም የሰው ልቡ ፊቱን ይለ​ው​ጠ​ዋል።

25 ደስ ያለው ልቡና ምል​ክቱ ብሩህ ገጽ ነው፥ ደክ​መህ የጥ​በ​ብን ምክር ታገ​ኛ​ለህ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች