Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ሲራክ 12 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በጎ ሥራ በሠ​ራህ ጊዜ የበ​ጎ​ነ​ት​ህን ዋጋ ታገኝ ዘንድ፥ በጎ ሥራ የም​ት​ሠ​ራ​ለ​ትን ዕወቅ።

2 ለጻ​ድቅ በጎ አድ​ርግ፥ ዋጋ​ህ​ንም ታገ​ኛ​ለህ፤ በእ​ርሱ ዘንድ ባታ​ገ​ኘው በፈ​ጣ​ሪው ዘንድ ታገ​ኛ​ለህ።

3 ኀጢ​አ​ትን በሚ​ሠ​ራና ምጽ​ዋ​ትን በማ​ይ​መ​ጸ​ውት ዘንድ፥ በጎ ሥራ የለም።

4 ኀጢ​አ​ተኛ እን​ዳ​ይ​ወ​ስ​ድ​ብህ ለጻ​ድቁ ስጥ።

5 ለድሃ መል​ካም አድ​ርግ፥ ለክፉ ግን አት​ስጥ፤ እርሱ እን​ዳ​ይ​ወ​ስ​ድ​ብ​ህና በገ​ን​ዘ​ብህ ድል እን​ዳ​ያ​ደ​ር​ግህ እን​ጀ​ራ​ህን ከል​ክ​ለው፥ በጎ ነገር ስላ​ደ​ረ​ግ​ህ​ለት ፋንታ በእ​ርሱ ዘንድ ክፋ​ትን እጥፍ ሆና ታገ​ኛ​ታ​ለ​ህና።

6 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኀጢ​አ​ተ​ኞች ሰዎ​ችን ይጠ​ላ​ቸ​ዋ​ልና፤ ክፉ ሰዎ​ች​ንም ይበ​ቀ​ላ​ቸ​ዋ​ልና።

7 ለኀ​ጢ​አ​ተኛ ከም​ት​ሰጥ ለጻ​ድቅ ስጥ፤ በደ​ስ​ታም ጊዜ ወዳ​ጅህ አያ​ም​ል​ጥህ።

8 በመ​ከ​ራ​ህም ጊዜ ጠላ​ትህ አይ​ሰ​ወ​ርህ።

9 ደስ​ታህ ጠላ​ቶ​ች​ህን ያሳ​ዝ​ና​ቸ​ዋል፤ ችግ​ር​ህም ወዳ​ጆ​ች​ህን አስ​ወ​ጥቶ ይሰ​ድ​ዳ​ቸ​ዋል።

10 የል​ቡ​ናው ክፋት እንደ ብረት ዝገት ነውና፤ ጠላ​ት​ህን ፈጽ​መህ አት​መ​ነው።

11 በተ​ቸ​ገ​ር​ህም ጊዜ እያ​መ​ሰ​ገነ ያገ​ለ​ግ​ል​ሃል፤ ሰው​ነ​ት​ህን አጽ​ናት፤ ከእ​ር​ሱም ተጠ​በቅ፤ እን​ደ​ዛገ መስ​ታ​ወት ትሆ​ን​በ​ታ​ለህ፤ ፈጽ​ሞም አይ​ች​ል​ህም።

12 እን​ዳ​ይ​ጎ​ዳህ ባጠ​ገ​ብህ አታ​ቁ​መው፥ በቦ​ታ​ህም አይ​ቀ​መጥ፤ ሹመ​ት​ህ​ንም እን​ዳ​ይ​ወ​ስ​ድ​ብህ በቀ​ኝህ አታ​ስ​ቀ​ም​ጠው። በመ​ጨ​ረ​ሻም ቃሌን ታው​ቀው ዘንድ አለህ፥ ምክ​ሬ​ንም ታስ​በ​ዋ​ለህ።

13 በእ​ባብ ለተ​ነ​ደፈ አስ​ማ​ተኛ፥ ወደ ክፉ አው​ሬም ለቀ​ረበ ሁሉ ማን ያዝ​ን​ለ​ታል?

14 ከኀ​ጢ​አ​ተ​ኛም ሰው ጋር የሚ​ሄድ፥ በኀ​ጢ​አ​ቱም የሚ​ተ​ባ​በር እን​ዲሁ ነው።

15 ጠላ​ትህ ከአ​ንተ ጋር አንድ ጊዜ ይቆ​ማል፥ ነገር ግን እስ​ክ​ት​መ​ለስ ድረስ አታ​የ​ውም፥ ከአ​ን​ተም ጋር አይ​ታ​ገ​ሥም።

16 ጠላ​ትህ በከ​ን​ፈሩ ቃሉን ያጣ​ፍ​ጥ​ል​ሃል፥ በልቡ ግን በጕ​ድ​ጓድ ውስጥ ይጥ​ልህ ዘንድ ይመ​ክ​ራል። ጠላ​ትህ በዐ​ይኑ ያለ​ቅ​ስ​ል​ሃል፥ ካሳ​ተህ በኋላ ግን ከደ​ምህ አይ​ጠ​ግ​ብም።

17 ብት​ቸ​ገ​ርም ከሁሉ አስ​ቀ​ድሞ በፊ​ትህ ታገ​ኘ​ዋ​ለህ፤ እን​ደ​ሚ​ረ​ዳ​ህም ከጫ​ማህ በታች ራሱን ዝቅ ያደ​ር​ጋል።

18 በእጁ ያጨ​በ​ጭ​ባል፤ ራሱ​ንም ይነ​ቀ​ን​ቃል፤ ከዚህ በኋላ ግን ፊቱን መልሶ ይጠ​ቃ​ቀ​ስ​ብ​ሃል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች