Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ኩፋሌ 8 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በዚህ ኢዮ​ቤ​ልዩ በሰ​ባ​ተ​ኛው ሱባዔ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዓመት መር​ከ​ቢቱ ባረ​ፈ​ች​በት ስሙ ሉባር በሚ​ባል ከአ​ራ​ራት ተራ​ሮች በአ​ንዱ ተራራ ላይ ኖኅ ወይ​ንን ተከለ።

2 በአ​ራ​ተ​ኛ​ውም ዓመት አፈራ፤ ፍሬ​ው​ንም ጠበቀ፤ በዚ​ያ​ውም ዓመት በሰ​ባ​ተ​ኛው ወር ፍሬ​ውን ለቀመ። ከእ​ር​ሱም ጠጅ ጥሎ በዕቃ አኖ​ረው፥ እስከ አም​ስ​ተ​ኛ​ውም ዓመት እስከ መጀ​መ​ሪ​ያው ወር መጀ​መ​ሪ​ያ​ዪቱ ቀን ድረስ ጠበ​ቀው።

3 ይህ​ች​ንም ቀን በደ​ስታ በዓል አደ​ረገ፥ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕ​ትን ሠዋ። የራ​ሱ​ንም ኀጢ​አት ያስ​ተ​ሰ​ር​ይ​በት ዘንድ ከላ​ሞች አንድ ወይ​ፈ​ንን፥ አንድ የበግ አው​ራን፥ ዓመት የሆ​ና​ቸው ሰባት በጎ​ችን፥ አን​ዲት የፍ​የል ጠቦ​ት​ንም ሠዋ።

4 ስለ ልጆ​ቹም አስ​ቀ​ድሞ ጠቦ​ትን ሠዋ፤ ከደ​ሙም በሠ​ራው መሠ​ዊያ ላይ ባለው ሥጋ ላይ አኖረ። የሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕ​ት​ንም በሠ​ዋ​በት መሠ​ዊያ ላይ ስቡን ሁሉ አጤሰ። ላሙ​ንና የበ​ጉን አውራ፥ በጎ​ቹ​ንም ሠውቶ ሥጋ​ቸ​ውን ሁሉ በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ አኖረ። በዘ​ይት የተ​ለ​ወሰ መሥ​ዋ​ዕ​ታ​ቸ​ው​ንም ሁሉ በላ​ያ​ቸው አኖረ።

5 ከዚ​ህም በኋላ በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ ባለው እሳት ላይ ወይ​ኑን ረጨ። አስ​ቀ​ድሞ ዕጣ​ኑን በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ አኖረ፤ እግ​አ​ብ​ሔር የሚ​ወ​ደ​ው​ንም በጎ መሥ​ዋ​ዕት ሠዋ። መሥ​ዋ​ዕ​ቱም ወደ አም​ላኩ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዐረገ፤ ከዚ​ህም ወይን ጠጥቶ ደስ አለው። ልጆ​ቹ​ንም ደስ አላ​ቸው።

6 በመ​ሸም ጊዜ ወደ ድን​ኳኑ ገብቶ ሰክሮ ተኛ፤ በድ​ን​ኳ​ኑም ተኝቶ ዕር​ቃ​ኑን ጣለ።

7 ካምም አባቱ ኖኅን ዕራ​ቁ​ቱን እንደ ሆነ አየ፤ ወጥ​ቶም በውጭ ለነ​በሩ ለሁ​ለቱ ወን​ድ​ሞቹ ነገ​ራ​ቸው።

8 ሴምም ልብ​ሱን ይዞ ተነሣ፤ እር​ሱና ያፌ​ትም ልብ​ሳ​ቸ​ውን ከጫ​ን​ቃ​ቸው አው​ር​ደው አለ​በ​ሱት፥ ፊታ​ቸ​ው​ንም ወደ ኋላ መል​ሰው የአ​ባ​ታ​ቸ​ውን ኀፍ​ረት ሸፈኑ።

9 ኖኅም ከእ​ን​ቅ​ልፉ በነቃ ጊዜ ታናሹ ልጁ በእ​ርሱ ላይ ያደ​ረ​ገ​በ​ትን ሁሉ ዐወቀ፥ ልጁ​ንም ረገ​መው፥ “የተ​ረ​ገመ ከነ​ዓን ለወ​ን​ድ​ሞቹ ተገዥ ባሪያ ይሁን” አለ።

10 ሴም​ንም መረ​ቀው፤ እን​ዲ​ህም አለ፥ “የሴም አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይመ​ስ​ገን፤ ከነ​ዓ​ንም ባሪ​ያው ይሁን፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የያ​ፌ​ትን ሀገር ያስ​ፋ​ለት፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በሴም ድን​ኳን ይደር፤ ከነ​ዓ​ንም ባሪ​ያው ይሁን።”

11 ካምም አባቱ ታና​ሹን ልጁን እንደ ረገ​መው ዐወቀ። ልጁ​ንም ረግ​ሞ​ታ​ልና ለእ​ርሱ ክፉ ነገር ሆነ​በት፤ እር​ሱም ከአ​ባቱ ተለየ፤ ልጆ​ቹም ከእ​ርሱ ጋር ነበሩ። እነ​ዚ​ህም ኩሽና ሜስ​ራ​ይም፥ ፉጥና ከነ​ዓን ናቸው። እር​ሱም ከተ​ማን አቀና፤ የከ​ተ​ማ​ዪ​ቱ​ንም ስም በሚ​ስቱ ስም አኤ​ል​ታ​ማክ ብሎ ጠራት።

12 ያፌ​ትም አይቶ በወ​ን​ድሙ ቀና፤ እር​ሱም ከተ​ማን አቀና፤ ስም​ዋ​ንም በሚ​ስቱ ስም አዶ​ታ​ኔ​ስስ ብሎ ጠራት።

13 ሴም ግን ከአ​ባቱ ከኖኅ ጋር ተቀ​መጠ፤ በአ​ባ​ቱም እጅ በተ​ራ​ራው ላይ ከተ​ማን አቀና፤ እር​ሱም ስም​ዋን በሚ​ስቱ በሴ​ዴ​ቄ​ተ​ል​ባብ ስም ጠራ።

14 እነ​ዚ​ህም ሦስቱ ከተ​ሞች፥ እነሆ፥ በሉ​ባር ተራራ አቅ​ራ​ቢያ ናቸው። ሴዴ​ቄ​ተ​ል​ባ​ብም በተ​ራ​ራው አን​ጻር በም​ሥ​ራቅ ናት፥ አኤ​ል​ታ​ማ​ክም በሰ​ሜን አን​ጻር ናት፤ አዶ​ታ​ኒ​ስ​ስም በም​ዕ​ራብ ናት።

15 የሴ​ምም ልጆች እነ​ዚህ ናቸው፥ ኤላ​ምና አሱር፥ አር​ፋ​ክ​ስ​ድም ሉድና አራ​ምም፥ እነ​ዚህ የጥ​ፋት ውኃ ከሆ​ነ​በት ከአ​ራ​ተ​ኛው ዓመት በኋላ የተ​ወ​ለዱ ናቸው። ያፌ​ትም ጎሜ​ር​ንና ማጎ​ግን፥ ያዋ​ን​ንና ቶቤ​ልን፥ ሞሳ​ክ​ንና ቴራ​ስን ወለደ። እነ​ዚህ ሁሉ የኖኅ ልጆች ናቸው።

16 ኖኅም በሃያ ስም​ን​ተ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ ለልጅ ልጆቹ ሥር​ዐ​ት​ንና ትእ​ዛ​ዝን፥ የሚ​ያ​ው​ቀ​ው​ንም ፍርድ ሁሉ ያዝዝ ጀመረ። እው​ነ​ት​ንም ያደ​ርጉ ዘንድ፥ የሰ​ው​ነ​ታ​ቸ​ው​ንም ኀፍ​ረት ይሸ​ፍኑ ዘንድ፥ የፈ​ጠ​ራ​ቸው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ያመ​ሰ​ግኑ ዘንድ፥ አባ​ትና እና​ታ​ቸ​ው​ንም ያከ​ብሩ ዘንድ፥ እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ቸ​ውም ባል​ን​ጀ​ራ​ቸ​ውን ይወ​ድዱ ዘንድ፥ ሰው​ነ​ታ​ቸ​ው​ንም ከዝ​ሙ​ትና ከር​ኵ​ሰት፥ ከበ​ደ​ልም ይጠ​ብቁ ዘንድ ያዝ​ዛ​ቸው ጀመር።

17 ትጉ​ሃን ከታ​ዘ​ዘ​ላ​ቸው ሕግ ወጥ​ተው ከሰው ልጆች ጋር ስላ​ደ​ረ​ጉት ዝሙት በእ​ነ​ዚህ በሦ​ስቱ ኀጢ​አ​ቶች በም​ድር ላይ የጥ​ፋት ውኃ ተደ​ር​ጎ​አ​ልና።

18 ከመ​ረ​ጡ​አ​ቸው ሴቶ​ችም ሁሉ ሚስ​ቶ​ችን አገቡ፥ አስ​ቀ​ድ​መ​ውም ርኵ​ሰ​ትን ሠሩ። ኀይ​ለ​ኞች ልጆ​ች​ንም ወለዱ፤ ሁሉም አይ​መ​ሳ​ሰ​ሉም ነበሩ።

19 እያ​ን​ዳ​ን​ዱም ባል​ን​ጀ​ራ​ውን ይበ​ላው ነበር። አር​በ​ኛ​ውም ናፊ​ልን ገደ​ለው፤ ናፊ​ልም ኢል​ዮ​ንን ገደ​ለው፥ ኢል​ዮ​ንም የሰ​ውን ልጅ ገደ​ለው። ሰውም ባል​ን​ጀ​ራ​ውን ገደ​ለው፤ ሁሉም ዐመ​ፅን ያደ​ርግ ዘንድ፥ ንጹሕ ደም​ንም ያፈ​ስስ ዘንድ ተመ​ለሰ። ምድ​ርም ዐመ​ፅን ተሞ​ላች፥ ከእ​ነ​ዚ​ህም ሁሉ በኋላ በአ​ው​ሬ​ዎ​ችና በወ​ፎች፥ በም​ድር ላይም በሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀ​ሰ​ውና በሚ​መ​ላ​ለ​ሰው ሁሉ ላይ በደሉ።

20 በም​ድ​ርም ላይ ብዙ ደም ፈሰሰ፤ የሰ​ውም ልቡ​ና​ውና ፈቃዱ በዘ​መኑ ሁሉ ከን​ቱና ክፉ ነገ​ርን ያስቡ ጀመር።

21 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ስለ ክፉ ሥራ​ቸው በም​ድር ሁሉ ፊት ሁሉን አጠፋ። በም​ድ​ርም ስላ​ፈ​ሰ​ሱት ደም ሁሉን ደመ​ሰሰ፤ “እኔና እና​ንተ ልጆች፥ ከእ​ኛም ጋር ወደ መር​ከብ የገ​ባው ሁሉ ቀረን።

22 በጥ​ፋት ሥራ ጸን​ታ​ችሁ ትኖሩ ዘንድ ጀም​ራ​ች​ኋ​ልና እና​ንተ በእ​ው​ነት ሥራ ጸን​ታ​ችሁ የም​ት​ኖሩ እን​ዳ​ል​ሆ​ና​ችሁ እነሆ፥ እኔ የቀ​ደመ ሥራ​ች​ሁን አየሁ። እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ችሁ ከባ​ል​ን​ጀ​ራ​ችሁ ትለ​ያ​ላ​ችሁ፤ እርስ በር​ሳ​ች​ሁም ትቀ​ና​ና​ላ​ችሁ።

23 ልጆች፥ አንዱ ከአ​ንዱ ጋር በአ​ን​ድ​ነት እን​ደ​ማ​ት​ኖሩ እኔ አያ​ለሁ፤ አጋ​ን​ን​ትም በእ​ና​ን​ተና በል​ጆ​ቻ​ችሁ ላይ እነሆ፥ ማሳት ጀመሩ።

24 አሁ​ንም እኔ ከሞ​ትሁ በኋላ በም​ድር ላይ የሰ​ውን ደም ታፈ​ስ​ሳ​ላ​ችሁ፤ እና​ን​ተም ከገጸ ምድር ትጠ​ፋ​ላ​ችሁ ብዬ እኔ ስለ እና​ንተ እፈ​ራ​ለሁ። የሰ​ውን ደም የሚ​ያ​ፈ​ስስ ሁሉና ብር​ንዶ የሚ​በላ ሁሉ፥ ሁሉም ከዚህ ዓለም ይጠ​ፋ​ሉና፤ ብር​ን​ዶ​ንም የሚ​በላ ደም​ንም የሚ​ያ​ፈ​ስስ ሁሉ በዚህ ዓለም አይ​ቀ​ር​ምና።

25 ወደ መቃ​ብር ይሄ​ዳ​ሉና፥ ቍርጥ ፍርድ ወዳ​ለ​በት ወደ ሲኦ​ልም ይወ​ር​ዳ​ሉና፥ ሁሉም በክፉ ሞት ተይ​ዘው ወደ ጨለ​ማው ጥልቅ ይጣ​ላ​ሉና፥ ከሰ​ማይ በታች ልጅ፥ የልጅ ልጅም በሕ​ይ​ወት አይ​ቀ​ር​ለ​ትም።

26 “ማን​ኛ​ው​ንም አው​ሬና እን​ስሳ፥ በም​ድር ላይ የሚ​በ​ር​ረ​ው​ንም ባረ​ዳ​ችሁ ጊዜ በዘ​መ​ና​ችሁ ሁሉ ከማ​ን​ኛ​ውም ደም፦ ደም ሁሉ በእ​ና​ንተ ላይ አይ​ታይ።

27 በም​ድር ላይ የሚ​ፈ​ስ​ሰ​ውን ደም በመ​ቅ​በር ስለ ሰው​ነ​ታ​ችሁ ምጽ​ዋት መጽ​ውቱ፤ ከደም ጋር የሚ​በ​ላም አት​ሁኑ። ሌሎ​ችም በፊ​ታ​ችሁ ደም እን​ዳ​ይ​በሉ ተጠ​ን​ቀቁ። እኔ እን​ደ​ዚህ ታዝ​ዣ​ለ​ሁና ደሙን ቅበሩ።

28 በእ​ና​ን​ተና በል​ጆ​ቻ​ችሁ ከሰው ሁሉ ጋር እመ​ሰ​ክ​ር​ባ​ች​ኋ​ለሁ። በም​ድር ላይ ደምን ከሚ​ያ​ፈ​ስስ ሰው ሁሉ ጋር በሰ​ው​ነ​ታ​ችሁ ደማ​ች​ሁን የሚ​መ​ረ​ም​ሩ​አ​ችሁ እን​ዳ​ይ​ሆኑ ነፍ​ስን ከሥጋ ጋር አት​ብ​ሉ​አት፤ ምድር በት​ው​ልዱ ሁሉ ደምን ባፈ​ሰሰ ሰው ደም የም​ት​ነጻ ስለ​ሆነ ምድር በላ​ይዋ ከፈ​ሰሰ ደም አት​ነ​ጻ​ምና።

29 “አሁ​ንም ልጆች፥ ስሙኝ፥ በም​ድር ሁሉ በእ​ው​ነት ፊት ጸን​ታ​ችሁ ትኖሩ ዘንድ፥ ክብ​ራ​ች​ሁም ከጥ​ፋት ውኃ ባዳ​ነኝ በአ​ም​ላኬ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ይገ​ለጥ ዘንድ ፍር​ድ​ንና ጽድ​ቅን ፍረዱ።

30 እነሆ፥ እና​ን​ተም ሄዳ​ችሁ ከተ​ሞ​ችን ታቀ​ና​ላ​ችሁ፤ በው​ስ​ጣ​ቸ​ውም በም​ድር ላይ ያለ​ውን ተክል ሁሉ ትተ​ክ​ላ​ላ​ችሁ። ተክ​ሉም ሁሉ በሦ​ስ​ተ​ኛው ዓመት የሚ​ያ​ፈ​ራ​ውን ፍሬ ሁሉ ለመ​ብ​ላት የማ​ይ​ለ​ቀም ይሆ​ናል።

31 በአ​ራ​ተ​ኛ​ውም ዓመት ፍሬው ይቀ​ደ​ሳል፤ ሰማ​ይ​ንና ምድ​ርን በፈ​ጠረ በል​ዑል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ተቀ​ባ​ይ​ነት ያለ​ው​ንም የፍ​ሬ​ውን መጀ​መ​ሪያ ይሠ​ዋሉ፥ የወ​ይ​ኑ​ንና የዘ​ይ​ቱን መጀ​መ​ሪያ፥ እንደ አዝ​መ​ራው መጀ​መ​ሪያ በሚ​ቀ​በ​ለው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊያ በፈ​ሳ​ሽ​ነት ያቀ​ር​ባሉ፤ የቀ​ረ​ው​ንም የቤተ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አገ​ል​ጋ​ዮች መሥ​ዋ​ዕ​ቱን በሚ​ቀ​በ​ል​በት በመ​ሠ​ዊ​ያው ፊት ይብ​ሉት።

32 እና​ንተ በእ​ው​ነ​ትና በሚ​ገባ ትተ​ዉት ዘንድ በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ዓመት ዕረ​ፍ​ትን አድ​ርጉ፤ እና​ን​ተም ትከ​ብ​ራ​ላ​ችሁ፤ ተክ​ላ​ች​ሁም ሁሉ የበጀ ይሆ​ናል። የአ​ባ​ታ​ችሁ አባት ሄኖክ ልጁ ማቱ​ሳ​ላን እን​ዲሁ አዝ​ዞ​ታ​ልና፤ ማቱ​ሳ​ላም ልጁ ላሜ​ህን አዝ​ዞ​ታ​ልና፤ ላሜ​ህም አባ​ቶቹ ያዘ​ዙ​ትን ሁሉ ለእኔ አዝ​ዞ​ኛ​ልና።

33 እኔም፥ ልጆች ሆይ፥ ሄኖክ ልጁን እን​ዳ​ዘ​ዘው አዝ​ዛ​ች​ኋ​ለሁ፤ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ኢዮ​ቤ​ልዩ በሕ​ይ​ወት ሳለ በሰ​ባ​ተ​ኛው ትው​ልድ ማቱ​ሳላ እስ​ከ​ሚ​ሞ​ት​ባት ቀን ድረስ ልጆ​ቹ​ንና የል​ጆ​ቹን ልጆች አዝዞ አዳኘ።”

34 በሃያ ዘጠ​ነ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ሱባዔ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዓመት አር​ፋ​ክ​ስድ ሚስት አገባ፤ ስም​ዋም ራሱ​እያ ይባ​ላል፤ ይህ​ች​ውም የኤ​ላም ልጅ የሱ​ሳን ልጅ ናት። በሦ​ስ​ተ​ኛው ዓመት በዚህ ሱባዔ ወንድ ልጅን ወለ​ደ​ች​ለት፤ ስሙ​ንም ቃይ​ናም አለው፤ ልጁም አደገ፤ አባ​ቱም መጽ​ሐ​ፍን አስ​ተ​ማ​ረው።

35 ከተ​ማ​ንም የሚ​ይ​ዝ​በት ቦታን ይፈ​ልግ ዘንድ ሄደ፤ የቀ​ደሙ ሰዎ​ችም በድ​ን​ጋይ የቀ​ረ​ፁ​ትን መጽ​ሐፍ አገኘ። በእ​ር​ስ​ዋም ያለ​ውን አን​ብቦ ተረ​ጐመ። የፀ​ሓ​ይ​ንና የጨ​ረ​ቃን፥ የከ​ዋ​ክ​ብ​ት​ንም ሰገል ከሰ​ማይ ምል​ክ​ቶች ጋር የሚ​መ​ለ​ከ​ቱ​በት የት​ጉ​ሃን ትም​ህ​ርት ሁሉ በእ​ር​ስዋ ስለ ነበር በእ​ር​ስዋ በተ​ጻ​ፈው በደለ።

36 እር​ሱም ጻፋት፥ የእ​ር​ስ​ዋ​ንም ነገር አል​ተ​ና​ገ​ረም። ስለ እር​ስዋ በእ​ርሱ እን​ዳ​ይ​ቈጣ የእ​ር​ስ​ዋን ነገር ለመ​ና​ገር ኖኅን ይፈ​ራ​ዋ​ልና።

37 በሠ​ላ​ሳ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ በሁ​ለ​ተ​ኛው ሱባዔ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዓመት ሚስ​ትን አገባ፤ ስም​ዋም ሜልካ ይባ​ላል፤ ይህ​ች​ውም የያ​ፌት ልጅ የአ​በ​ዳይ ልጅ ናት።

38 በአ​ራ​ተ​ኛ​ውም ዓመት ወንድ ልጅን ወለ​ደ​ች​ለት፦ ስሙ​ንም ሳላ አለው፤ መል​እ​ክ​ትን ተል​ኬ​አ​ለሁ ብሎ​አ​ልና፤ ሳላም አደገ፤ በሠ​ላሳ አን​ደ​ኛ​ውም ኢዮ​ቤ​ልዩ በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዓመት ሚስ​ትን አገባ ስም​ዋም ሙአክ ይባ​ላል፤ ይህ​ች​ውም የአ​ባቱ ወን​ድም የኬ​ሴድ ልጅ ናት።

39 በአ​ም​ስ​ተ​ኛ​ውም ዓመት ወንድ ልጅን ወለ​ደ​ች​ለት፤ ስሙ​ንም ኤቦር አለው። እር​ሱም በሠ​ላሳ ሁለ​ተ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ በሰ​ባ​ተ​ኛው ሱባዔ በሦ​ስ​ተ​ኛው ዓመት ሚስ​ትን አገባ፤ ስም​ዋም አዙ​ራድ ይባ​ላል፥ ይህ​ች​ውም የአ​ብ​ሮድ ልጅ ናት።

40 በስ​ድ​ስ​ተ​ኛ​ውም ዓመት ወንድ ልጅን ወለ​ደ​ች​ለት፤ ስሙ​ንም ፋሌክ አለው፤ በተ​ወ​ለ​ደ​በት ዘመን የኖኅ ልጆች ምድ​ርን ሊካ​ፈሉ ጀም​ረ​ዋ​ልና፤ ስለ​ዚ​ህም ስሙን ፋሌክ ብሎ ጠራው፤ እርስ በር​ሳ​ቸ​ውም አስ​ተ​ካ​ክ​ለው ተካ​ፈሉ፥ ለኖ​ኅም ነገ​ሩት።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች