Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ኩፋሌ 7 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በዐ​ሥ​ረ​ኛው ወር መባ​ቻም የተ​ራ​ሮች ራሶች ታዩ፤ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር መባ​ቻም ምድር ታየች፤ ውኃ​ዎ​ችም በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ በሰ​ባ​ተ​ኛው ዓመት ከም​ድር ላይ ደረቁ። በዐ​ሥራ ሰባ​ተ​ኛ​ውም ቀን በሁ​ለ​ተ​ኛው ወር ምድር ደረ​ቀች።

2 በሃያ ሰባ​ተ​ኛ​ውም ቀን መር​ከ​ቢ​ቱን ከፈ​ታት፤ ከው​ስ​ጥ​ዋም አራ​ዊ​ት​ንና ወፎ​ችን፥ የሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀ​ሰ​ው​ንም ሁሉ ሰደደ። በሦ​ስ​ተ​ኛ​ውም ወር መባቻ ኖኅ ከመ​ር​ከብ ወጣ። በዚ​ህም ተራራ ላይ መሠ​ዊ​ያን ሠራ፤ ለም​ድ​ርም አስ​ተ​ሰ​ረየ። ከኖኅ ጋር በመ​ር​ከብ ካሉት በቀር በእ​ር​ስዋ ያለው ሁሉ ጠፍ​ቶ​አ​ልና የፍ​የል ጠቦት ሠውቶ በደሙ የም​ድ​ርን ኀጢ​አት ሁሉ አስ​ተ​ሰ​ረየ።

3 ስቡ​ንም በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ አጤሰ። ላምን ፍየ​ል​ንና የበግ አው​ራን፥ ጨውን፥ ርግ​ብ​ንና ዋኖ​ስ​ንም ሠውቶ በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ ስቡን አሻ​ተተ። በዘ​ይት የታሸ መሥ​ዋ​ዕ​ት​ንም በእ​ነ​ርሱ ላይ ጨመረ።

4 ደሙ​ንና ወይ​ኑ​ንም አም​ጥቶ በሁሉ ላይ ዕጣን ጨመ​ረ​በት። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የሚ​ወ​ደ​ውን በጎ መዓዛ አድ​ርጎ አቀ​ረበ።

5 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በጎ መዓ​ዛ​ውን ተቀ​በ​ለው፤ የጥ​ፋ​ትም ውኃ ምድ​ርን እን​ዳ​ያ​ጠፋ ከእ​ርሱ ጋር ቃል ኪዳን አደ​ረገ። እን​ዲ​ህም አለ፥ “በም​ድ​ርም ዘመን ሁሉ ዘርና አዝ​መራ አይ​ቋ​ረ​ጥም፤ ብር​ድና ሙቀት፥ በጋና ክረ​ምት፥ ቀንና ሌሊት ሥር​ዐ​ታ​ቸ​ውን አይ​ለ​ው​ጡም። ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ሙም አይ​ቋ​ረ​ጡም።

6 “እና​ን​ተም ብዙ፥ በም​ድ​ርም የብዙ ብዙ ሁኑ፥ በላ​ይ​ዋም ብዙ፥ ለበ​ረ​ከ​ትም ሁኑ፤ ከእ​ና​ን​ተም የተ​ነሣ መፍ​ራ​ት​ንና መን​ቀ​ጥ​ቀ​ጥን በም​ድ​ርና በባ​ሕር ውስጥ ባሉ ሁሉ ላይ አመ​ጣ​ለሁ።

7 እነሆ፥ አው​ሬ​ዎ​ች​ንና ከብ​ቶ​ችን ሁሉ፥ በክ​ንፍ የሚ​በ​ሩ​ት​ንና በም​ድ​ርና በባ​ሕር ውስጥ የሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀ​ሱ​ትን ዓሣ​ዎ​ችን ሰጠ​ኋ​ችሁ፥ ሁሉ​ንም ትበሉ ዘንድ ልም​ላ​ሜ​ውን ለም​ግ​ብ​ነት ሰጠ​ኋ​ችሁ።

8 ነገር ግን ደም የነ​ፍስ ማደ​ሪያ ነውና ከሰ​ው​ነ​ታ​ችሁ መካ​ከል ደማ​ች​ሁን እን​ዳ​ል​ፈ​ልግ ደመ ነፍስ ያለ​ች​በ​ትን ሥጋ አት​ብሉ። ከሰ​ውም ሁሉ እጅ፥ ከአ​ራ​ዊ​ትም ሁሉ እጅ የሰ​ውን ደም እመ​ራ​መ​ራ​ለሁ፤ የሰ​ው​ንም ደም ያፈ​ሰሰ ደሙ ይፈ​ስ​ሳል፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አዳ​ምና ሔዋ​ንን በእ​ርሱ መልክ ፈጥ​ሮ​አ​ቸ​ዋ​ልና እና​ንተ ብዙ፤ በም​ድ​ርም ላይ የብዙ ብዙ ሁኑ” አላ​ቸው።

9 ኖኅና ልጆ​ቹም በሥ​ጋው ሁሉ ያለ ብር​ን​ዶ​ውን ሁሉ እን​ዳ​ይ​በሉ ማሉ። በም​ድር ዘመን ሁሉ በዚህ ወራት በዘ​ለ​ዓ​ለ​ማዊ አም​ላክ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ቃል ኪዳን ገባ።

10 ስለ​ዚ​ህም፥ “አንተ ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ጋር በዚህ ወራት በተ​ራ​ራው ላይ በመ​ሐላ ቃል ኪዳን ታደ​ርግ ዘንድ ተና​ገ​ረህ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በዘ​መኑ ሁሉ ከእ​ነ​ርሱ ጋር ስለ አደ​ረ​ገው ቃል ኪዳን በላ​ያ​ቸው ደምን ትረ​ጫ​ለህ።

11 በም​ድ​ርም ዘመን ሁሉ የወ​ፎ​ች​ንና የአ​ው​ሬ​ዎ​ችን ሥጋ ሁሉ እን​ዳ​ት​በሉ በዘ​መኑ ሁሉ ትጠ​ብ​ቁ​አት ዘንድ ይህች ምስ​ክር በእ​ና​ንተ ላይ የተ​ጻ​ፈች ናት።

12 በም​ድ​ርም ዘመን ሁሉ የአ​ው​ሬ​ውን፥ የከ​ብ​ቶ​ች​ንና የወ​ፎ​ችን ሥጋ ብር​ን​ዶ​ውን የበላ ሰው እር​ሱና ዘሩ ከም​ድር ይጠ​ፋሉ።

13 አን​ተም በዘ​መኑ ሁሉ በአ​ም​ላ​ካ​ችን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ስማ​ቸ​ውና ዘራ​ቸው ጸንቶ ይኖር ዘንድ ብር​ን​ዶ​ውን ሁሉ እን​ዳ​ይ​በሉ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች እዘ​ዛ​ቸው።

14 በቀኑ ሁሉ በመ​ሠ​ዊ​ያው አን​ጻር በደም ስለ እና​ንተ እየ​ለ​መኑ እን​ዲ​ኖሩ ለልጅ ልጅ ይጠ​ብ​ቁት ዘንድ የዘ​ለ​ዓ​ለም ሕግ ነውና ለዚህ ሕግ የዘ​መን ፍጻሜ የለ​ውም። ይጠ​ብ​ቁ​ትም ዘንድ እን​ዳ​ይ​ጠፉ ማታና ጥዋት ስለ እነ​ርሱ ሁል​ጊዜ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውን ያስ​ተ​ሰ​ር​ያሉ።

15 “ዳግ​መ​ኛም በም​ድር ላይ ጥፋት እን​ዳ​ይ​ሆን ለኖ​ኅና ለል​ጆቹ የቃል ኪዳ​ኑን ምል​ክት ሰጣ​ቸው፤ እር​ስ​ዋ​ንም ዳግ​መኛ ለማ​ጥ​ፋት በዘ​መኑ ሁሉ በም​ድር ላይ የጥ​ፋት ውኃ እን​ዳ​ይ​ሆን ለዘ​ለ​ዓ​ለም ለቃል ኪዳኑ ምል​ክት ቀስ​ቱን በደ​መና ውስጥ ሰጠ።

16 “ስለ​ዚ​ህም በዘ​መኑ ሁሉ ለአ​ዲስ ኪዳን በየ​ዓ​መቱ አንድ ጊዜ በዚህ ወር የሱ​ባ​ዔ​ያ​ትን በዓል የሚ​ያ​ደ​ርጉ ይሆኑ ዘንድ ተሠራ፤ በሰ​ማይ ጽላ​ትም ተጻፈ።

17 ይህ​ችም በዓል ከፍ​ጥ​ረት ቀን ጀምሮ እስከ ኖኅ ዘመን ድረስ በሰ​ማይ ስት​ሠራ ኖረች፤ ይኸ​ውም ሃያ ሰባት ኢዮ​ቤ​ል​ዩና አም​ስት የዓ​መት ሱባዔ ነው። ኖኅና ልጆ​ቹም፥ ኖኅ እስ​ከ​ሚ​ሞ​ት​ባት ቀን ድረስ ሰባት ኢዮ​ቤ​ል​ዩና አንድ የዓ​መት ሱባዔ ጠበ​ቁት።

18 ኖኅ ከሞተ በኋ​ላም እስከ አብ​ር​ሃም ዘመን ድረስ ልጆቹ ሕግን አፈ​ረሱ፤ ብር​ን​ዶ​ው​ንም በሉ። ነገር ግን አብ​ር​ሃም ብቻ ሕግን ጠበቀ፤ ይስ​ሐ​ቅና ያዕ​ቆ​ብም እስከ አንተ ዘመን ድረስ ጠበ​ቁት። በዘ​መ​ን​ህም በዚህ ተራራ እስ​ካ​ድ​ሳ​ቸው ድረስ የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ሕግን ዘነጉ።

19 አን​ተም የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች እዘ​ዛ​ቸው፤ ይህ​ች​ንም በዓል በት​ው​ል​ዳ​ቸው ሁሉ ለእ​ነ​ርሱ እንደ ታዘዘ ይጠ​ብ​ቁ​አት። በሱ​ባዔ የም​ት​ደ​ረግ በዓል ናትና በዓ​መት አንድ ቀን በዚህ ወር ይህ​ችን በዓል ያድ​ርጉ።

20 የመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ውም አዝ​መራ የሚ​ሰ​በ​ሰ​ብ​ባት በዓል ናትና። ይህ​ች​ውም ሁለት ቀን በዓል የሚ​ያ​ደ​ር​ጉ​ባት ሁለት አይ​ነት በዓል ናት። በየ​ጊ​ዜ​ዋም ታደ​ር​ጋት ዘንድ በጻ​ፍ​ሁ​ልህ በዚህ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው የሕግ መጽ​ሐፍ ጽፌ​ል​ሃ​ለ​ሁና ስለ እር​ስዋ ሥራዋ እንደ ተጻ​ፈና እንደ ተቀ​ረፀ ከዓ​መት አንድ ቀን ጠብ​ቃት።

21 የታ​ሰ​ቡም ይሆኑ ዘንድ፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች በየ​ወ​ገ​ና​ቸው ለእ​ያ​ን​ዳ​ንዱ ዓመት በዚህ ወር አንድ ቀን ያደ​ር​ጉ​አት ዘንድ ቍር​ባ​ኑን ነገ​ር​ሁህ።

22 “በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር መባቻ፥ በአ​ራ​ተ​ኛ​ውም ወር መባቻ፥ በሰ​ባ​ተ​ኛ​ውም ወር መባቻ፥ በዐ​ሥ​ረ​ኛ​ውም ወር መባቻ እነ​ዚህ የመ​ታ​ሰ​ቢያ ቀኖች ናቸው። በአ​ራ​ቱም ክፍለ ዓመት፥ ጊዜ ያላ​ቸው ቀኖች ናቸው፤ እነ​ዚ​ህም ለስ​ም​ን​ተ​ኛው ዓመት የተ​ጻ​ፉና የተ​ዘ​ጋጁ ናቸው።

23 ኖኅም እነ​ርሱ ለእ​ርሱ መታ​ሰ​ቢያ እስ​ኪ​ሆ​ኑ​ለት ድረስ በዓ​ላ​ትን ለልጅ ልጅ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ሠራ​ቸው።

24 በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር መባቻ ለራሱ መር​ከ​ብን ይሠራ ዘንድ ተነ​ገ​ረው፤ በእ​ር​ስ​ዋም ምድር ደረ​ቀች፤ መስ​ኮ​ቱ​ንም ከፍቶ ምድ​ርን አየ።

25 በአ​ራ​ተ​ኛው ወር መባቻ የታ​ች​ኛው የጥ​ልቁ ምንጭ አፍ ተዘጋ። የሰ​ማ​ዩም ሻሻቴ ተገታ።

26 በሰ​ባ​ተ​ኛው ወር መባቻ በም​ድር ያለ የም​ንጭ ውኃ ጕድ​ጓድ ሁሉ ተከ​ፈተ፤ ውኃ​ዎ​ችም ወደ ታች​ኛው ጥልቅ ይወ​ርዱ ጀመር።

27 በዐ​ሥ​ረ​ኛ​ውም ወር መባቻ የተ​ራ​ሮች ራሶች ታዩ፥ ኖኅም ደስ አለው፤ ስለ​ዚ​ህም እነ​ር​ሱን እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ ለመ​ታ​ሰ​ቢያ በዓ​ላት አደ​ረ​ጋ​ቸው። እነ​ዚህ እን​ዲህ የተ​ሠሩ ናቸው፤ ወደ ሰማይ ጽላ​ትም ያወ​ጡ​አ​ቸ​ዋል።

28 ከእ​ነ​ር​ሱም እያ​ን​ዳ​ን​ድዋ ከዚ​ች​ኛ​ዪቱ እስ​ከ​ዚ​ያ​ች​ኛ​ዪቱ መታ​ሰ​ቢያ፥ ከመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ዪቱ እስከ ሁለ​ተ​ኛ​ዪቱ፥ ከሁ​ለ​ተ​ኛ​ዪቱ እስከ ሦስ​ተ​ኛ​ዪቱ፥ ከሦ​ስ​ተ​ኛ​ዪቱ እስከ አራ​ተ​ኛ​ዪቱ ድረስ ዐሥራ ሦስት ሱባዔ ናቸው።

29 የት​እ​ዛ​ዛት ቀኖች ሁሉ ቀን የሚ​ቈ​ጠ​ር​ባ​ቸው አምሳ ሁለት ሱባዔ ይሆ​ናሉ። ፍጹም የሆነ ዓመቱ ሁሉ እን​ዲህ ተቀ​ር​ፆና ተቈ​ጥሮ በሰ​ማይ ጽላት ተጻፈ። አንድ ዓመ​ትና ሁለት ዓመት፥ ሦስት ዓመ​ትም መተ​ላ​ለፍ የለ​ውም።

30 አን​ተም የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች በዓ​መቱ በዚህ ቍጥር ሦስት መቶ ስድሳ አራት ቀንን ይጠ​ብቁ ዘንድ እዘ​ዛ​ቸው፤ ፍጹም ዓመ​ትም ይሆ​ናል። ጊዜ​ው​ንም ከቀ​ኑና ከበ​ዓሉ አሳ​ል​ፈው አያ​ጥፉ። ሁሉ እንደ ምስ​ክ​ር​ነ​ታ​ቸው ይደ​ር​ስ​ባ​ቸ​ዋ​ልና ቀኑን አያ​ስ​ቀሩ፤ በዓ​ሉ​ንም አያ​ጥፉ።

31 ቢተ​ላ​ለ​ፉ​አ​ቸ​ውም፥ እንደ እርሱ ትእ​ዛ​ዝም ባያ​ደ​ር​ጉ​አ​ቸው ያን ጊዜ ሁሉም ጊዜ​ዎ​ቻ​ቸ​ውን ያጠ​ፋሉ።

32 ዓመ​ታ​ትም ከዚህ ወደ​ዚያ ይለ​ዋ​ወ​ጣሉ፤ ጊዜ​ያ​ትም ይጠ​ፋሉ፤ ዓመ​ታ​ቱም ይለ​ዋ​ወ​ጣሉ፤ ሥር​ዐ​ታ​ቸ​ው​ንም ያፈ​ር​ሳሉ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ሁሉ ይዘ​ነ​ጋሉ። የዓ​መ​ታ​ት​ንም መን​ገድ አያ​ገ​ኙም፤ መባ​ቻ​ውን ይረ​ሳሉ፤ ጊዜ​ው​ንና ሱባ​ዔ​ውን፥ የዘ​መ​ኑ​ንም ሥር​ዐት ሁሉ ያፈ​ር​ሳሉ።

33 እኔ አው​ቃ​ለ​ሁና፥ እን​ግ​ዲህ ወዲህ እኔ እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ፤ እን​ዲህ ያለ መጽ​ሐፍ በፊቴ ተጽ​ፎ​አ​ልና፥ የም​ነ​ግ​ርህ ከልቤ አይ​ደ​ለም፤ ከሳቱ በኋላ አእ​ም​ሮ​አ​ቸ​ው​ንም ካጡ በኋላ የቃል ኪዳ​ኑን በዓል እን​ዳ​ይ​ረሱ፥ በአ​ሕ​ዛብ በዓ​ላ​ትም እን​ዳ​ይ​ሄዱ የዘ​መኑ አከ​ፋ​ፈል በሰ​ማይ ጽላት ተጻፈ።

34 “እር​ስዋ ጊዜ​ያ​ትን ትለ​ው​ጣ​ለ​ችና፥ ከዓ​መ​ታ​ትም ለዓ​መት ዐሥር ቀን ትቀ​ድ​ማ​ለ​ችና፥ በጨ​ረቃ አጐ​ዳ​ደል ጨረ​ቃን የሚ​መ​ለ​ከቱ ይሆ​ናሉ።

35 ስለ​ዚህ ሥር​ዐ​ትን ከለ​ወጡ በኋላ ዓመ​ታት ይመ​ጡ​ላ​ቸ​ዋል፤ ምስ​ክር የም​ት​ሆን ቀን​ንም የተ​ና​ቀች ያደ​ር​ጋሉ። የረ​ከ​ሰ​ች​ው​ምን ቀን በዓል ያደ​ር​ጋሉ፤ ሁሉ​ንም ይቀ​ላ​ቅ​ላሉ፤ የተ​ቀ​ደ​ሱ​ትን ቀናት የረ​ከሱ፥ የረ​ከ​ሱ​ት​ንም ቀናት ለቅ​ድ​ስና ያደ​ር​ጋሉ፤ ወራ​ቶ​ች​ንና ሱባ​ዔ​ዎ​ችን፥ በዓ​ላ​ቱ​ንና ኢዮ​ቤ​ላ​ቱን ይስ​ታ​ሉና።

36 ስለ​ዚ​ህም እኔ አዝ​ዝ​ሃ​ለሁ፤ ልጆ​ችህ አንተ ከሞ​ትህ በኋላ ሦስት መቶ ስድሳ አራ​ቱን ቀን ብቻ ዓመ​ትን እን​ዳ​ያ​ደ​ርጉ ሥር​ዐ​ትን ይለ​ው​ጣ​ሉና ታዳ​ኝ​ባ​ቸው ዘንድ አዳ​ኝ​ብ​ሃ​ለሁ።

37 ስለ​ዚ​ህም የወ​ሩን መባ​ቻና ሱባ​ዔ​ውን፥ ጊዜ​ው​ንና በዓ​ላ​ቱን ይስ​ታሉ፤ ከሰው ሁሉ ጋር ብር​ን​ዶ​ውን ሁሉ ይበ​ላሉ።”

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች