Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ኩፋሌ 6 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በዚ​ህም ሱባዔ ወንድ ልጅን ወለ​ደ​ች​ለት፥ ከሥ​ራዬ ሁሉና ከኀ​ዘኔ ሁሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከረ​ገ​ማት ምድር የሚ​ያ​ረ​ጋ​ጋኝ ነው ሲል ስሙን ኖኅ አለው።

2 በዐ​ሥራ ዘጠ​ነ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ መጨ​ረሻ በሰ​ባ​ተ​ኛው ሱባዔ በስ​ድ​ስ​ተ​ኛው ዓመት አዳም ሞተ። ልጆ​ቹም ሁሉ በተ​ፈ​ጠ​ረ​በት ምድር ቀበ​ሩት።

3 እር​ሱም አስ​ቀ​ድሞ በም​ድር ተቀ​በረ፤ ከሺህ ዓመ​ትም ሰባ ዓመ​ትን አጐ​ደለ። ይህ​ች​ውም በሰ​ማይ ምስ​ክር እንደ አን​ዲት ቀን ነበ​ረች።

4 “ከእ​ርሱ በም​ት​በ​ሉ​በት ቀን ትሞ​ታ​ላ​ችሁ” ተብ​ሎ​አ​ልና ስለ​ዚህ ዕው​ቀ​ትን የሚ​ያ​ሳ​ውቅ ዕፅን ስለ በላ ተጻፈ፤ በእ​ር​ስዋ ሞቶ​አ​ልና ስለ​ዚህ ነገር የአ​ን​ዲ​ቱን ቀን ዓመ​ቶች አል​ጨ​ረ​ሰም።

5 በዚህ ኢዮ​ቤ​ልዩ መጨ​ረሻ ከአ​ንድ ዓመት በኋላ ቃየን ሞተ፤ ቤቱ በላዩ ተናደ፤ በቤ​ቱም ውስጥ በድ​ን​ጋ​ዮች ሞተ። አቤ​ልን በድ​ን​ጋይ ገድ​ሎ​ታ​ልና በእ​ው​ነት ፍርድ በድ​ን​ጋይ ሞተ።

6 ስለ​ዚህ ሰው ባል​ን​ጀ​ራ​ውን በሚ​ገ​ድ​ል​በት መሣ​ሪያ ይሞት ዘንድ እን​ዳ​ቈ​ሰ​ለ​ውም ያቈ​ስ​ሉት ዘንድ በሰ​ማይ ጽላት ተጻፈ።

7 በሃያ አም​ስ​ተ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ ኖኅ ሚስት አገባ። ስም​ዋም አም​ዛራ ይባ​ላል። ይህ​ች​ውም የእ​ኅቱ ልጅ የራ​ዚ​ኤል ልጅ ናት፤ ሚስ​ትም ልት​ሆ​ነው አገ​ባት። በመ​ጀ​መ​ሪ​ያም ዓመት በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ በሦ​ስ​ተ​ኛው ዓመት ሴምን ወለ​ደ​ች​ለት። በአ​ም​ስ​ተ​ኛ​ውም ዓመት ካምን ወለ​ደ​ች​ለት።

8 በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዓመት በስ​ድ​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ ያፌ​ትን ወለ​ደ​ች​ለት።

9 የአ​ዳም ልጆች በም​ድር ላይ ይበዙ ዘንድ በጀ​መሩ ጊዜ እን​ዲህ ሆነ፤ ሴቶች ልጆች ተወ​ለ​ዱ​ላ​ቸው። የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መላ​እ​ክ​ትም በዚህ ኢዮ​ቤ​ልዩ በአ​ን​ዲቱ ዓመት እነ​ዚ​ህን አዩ​አ​ቸው። እነ​ዚያ ላዩ​አ​ቸው መልከ መል​ካ​ሞች ነበ​ሩና ከመ​ረ​ጡ​አ​ቸው ሁሉ ሚስ​ቶች ሊሆ​ኑ​አ​ቸው ወሰ​ዱ​አ​ቸው፤ ወን​ዶች ልጆ​ች​ንም ወለ​ዱ​ላ​ቸው፤ እነ​ዚ​ህም ረዓ​ይት ናቸው።

10 ኀጢ​አ​ትም በም​ድር ላይ በዛች፤ ሥጋ ለባ​ሹም ሁሉ ከሰው ጀምሮ እስከ እን​ስ​ሳና እስከ አራ​ዊት እስከ ወፎ​ችም፥ በም​ድር ላይ እስ​ከ​ሚ​ኖ​ረ​ውም ሁሉ ድረስ መን​ገ​ዱን አጠፋ። ሁሉም መን​ገ​ዳ​ቸ​ው​ንና ሥር​ዐ​ታ​ቸ​ውን አጠፉ። እርስ በር​ሳ​ቸ​ውም ይበ​ላሉ ጀመር። ኀጢ​አ​ትም በም​ድር ላይ በዛች። የሰ​ዎ​ችም ሁሉ ዐሳብ፥ በዘ​መኑ ሁሉ እን​ዲህ ክፉ ሆነ።

11 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ምድ​ርን ተመ​ለ​ከ​ታት፤ እነ​ሆም፥ ጠፍታ ነበር፤ ሰውም ሁሉ ሥር​ዐ​ቱን አጠፋ፥ ሁላ​ቸ​ውም በም​ድር ላይ ያለ​ውን ሁሉ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት አከ​ፉት፤ እር​ሱም ሰው​ንና በም​ድር ላይ የፈ​ጠ​ረ​ውን የሥጋ ወገ​ንን ሁሉ አጠ​ፋ​ዋ​ለሁ አለ።

12 ኖኅ ብቻ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ባለ​ም​ዋ​ል​ነ​ትን አገኘ። ወደ ምድር በሰ​ደ​ዳ​ቸው መላ​እ​ክቱ ግን ተቈጣ፤ ከሥ​ል​ጣ​ና​ቸ​ውም ለይቶ ፈጽሞ ያጠ​ፋ​ቸው ዘንድ አዘዘ። በም​ድር ጥልቅ ውስ​ጥም አስ​ረን እና​ግ​ዛ​ቸው ዘንድ አዘ​ዘን።

13 እነ​ር​ሱም እነሆ፥ በመ​ካ​ከ​ላ​ቸው ተግ​ዘ​ዋል፤ ብቻ​ቸ​ው​ንም ነበሩ። ከፊ​ቱም በሰ​ይፍ ያጠ​ፋ​ቸው ዘንድ፥ ከሰ​ማይ በታ​ችም ያር​ቃ​ቸው ዘንድ በል​ጆ​ቻ​ቸው ላይ ቃል ወጣ።

14 “እነ​ርሱ ሥጋ​ው​ያን ናቸ​ውና መን​ፈሴ በሰው ላይ ለዘ​ለ​ዓ​ለም አያ​ድ​ርም። ዕድ​ሜ​ያ​ቸ​ውም መቶ ሃያ ዓመት ይሁን” አለ።

15 እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ቸው ባል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ቸ​ውን ይገ​ድሉ ዘንድ በመ​ካ​ከ​ላ​ቸው ሰይ​ፍን ሰደደ። ሁሉም በሰ​ይፍ እስ​ኪ​ጠፉ ድረስ አንዱ ሌላ​ውን ይገ​ድል ዘንድ ጀመሩ፤ ከም​ድ​ርም ጠፉ፤ አባ​ቶ​ቻ​ቸው ግን ይመ​ለ​ከቱ ነበር።

16 ከዚህ በኋላ መን​ገ​ዳ​ቸ​ውን ባፋ​ለሱ ሁሉ ላይ ፍርድ ሊሆን እስከ ታላቋ የፍ​ርድ ቀን ድረስ በም​ድር ጥልቅ ውስጥ ተጋዙ። ሥራ​ቸ​ውም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ነው፤ ከቦ​ታ​ቸ​ውም ሁሉን አጠፋ፥ በኀ​ጢ​አ​ታ​ቸ​ውም ሁሉ ያል​ተ​ፈ​ረ​ደ​በት ከእ​ነ​ርሱ አንድ ስንኳ አል​ቀ​ረም።

17 በፍ​ጥ​ረ​ታ​ቸው ሁሉ እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ እን​ዳ​ይ​በ​ድሉ፥ ሁሉም በየ​ወ​ገኑ በዘ​መኑ ሁሉ የጽ​ድቅ ሥራን እን​ዲ​ሠራ ለፍ​ጥ​ረቱ ሁሉ አዲ​ስና እው​ነ​ተኛ ፍጥ​ረ​ትን ፈጠ​ረ​ላ​ቸው።

18 የሁ​ሉም ቅጣት ተዘ​ጋጀ፥ በሰ​ማ​ይም ጽላት ያለ ዐመፃ ተጻፈ። ሁሉም ጸን​ተው ይኖ​ሩ​ባት ዘንድ ከተ​ሠ​ራ​ች​ላ​ቸው ሥር​ዐ​ታ​ቸው የወጡ ናቸው።

19 ጸን​ተው ባይ​ኖ​ሩ​ባ​ትም ለፍ​ጥ​ረቱ ሁሉ ለየ​ወ​ገ​ኑም ሁሉ ፍርድ ተጻፈ። በሰ​ማ​ይና በም​ድር፥ በብ​ር​ሃ​ንና በጨ​ለማ፥ በሲ​ኦ​ልና በጥ​ል​ቅም፥ በጨ​ለ​ማም ምንም የለም።

20 ፍር​ዳ​ቸ​ውም ሁሉ ተዘ​ጋጀ፥ የተ​ቀ​ረ​ፀና የተ​ጻ​ፈም ነው። ስለ​ዚ​ህም ታላ​ቁን እንደ ታላ​ቅ​ነቱ፥ ታና​ሹ​ንም እንደ ታና​ሽ​ነቱ እያ​ን​ዳ​ን​ዱን እንደ ኀጢ​አቱ ይፈ​ር​ድ​በ​ታል።

21 እርሱ ፊት አይቶ የሚ​ያ​ደላ አይ​ደ​ለም። ለእ​ያ​ን​ዳ​ን​ዱም ፍርድ አደ​ር​ጋ​ለሁ ባለ ጊዜ እርሱ መማ​ለ​ጃን የሚ​ቀ​በል አይ​ደ​ለም፤ እያ​ን​ዳ​ን​ዱም በም​ድር ያለ ሰው ያለ​ውን ሁሉ ቢሰጥ ፊትን አይቶ አያ​ደ​ላም፤ የእ​ው​ነት ዳኛ ነውና ከእ​ርሱ መማ​ለጃ አይ​ቀ​በ​ልም።

22 ይህ በእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ላይ ተጽፎ ተሠራ። በእ​ው​ነ​ትም ወደ እርሱ ከተ​መ​ለሱ በደ​ላ​ቸ​ውን ሁሉ ይቅር ይላ​ቸ​ዋል። ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ው​ንም ሁሉ ያስ​ተ​ሰ​ር​ይ​ላ​ቸ​ዋል።

23 ከኀ​ጢ​አ​ታ​ቸ​ውም ሁሉ የተ​መ​ለሱ ሰዎች ሁሉ በየ​ዓ​መቱ አንድ ጊዜ ይቅር ይባሉ ዘንድ ተጽፎ ተሠራ። ከጥ​ፋት ውኃም አስ​ቀ​ድሞ ሥር​ዐ​ታ​ቸ​ው​ንና ምክ​ራ​ች​ውን ባጠፉ ሰዎች ሁሉ ላይ ተጻፈ።

24 በእ​ርሱ ምክ​ን​ያት ከጥ​ፋት ውኃ ስላ​ዳ​ና​ቸው ልጆቹ እርሱ ባለ​ም​ዋ​ል​ነ​ትን አግ​ኝ​ቶ​አ​ልና ከኖኅ ብቻ በቀር እነ​ርሱ ባለ​ም​ዋ​ል​ነ​ትን አላ​ገ​ኙም። ስለ እር​ሱም እንደ ታዘዘ በመ​ን​ገዱ ሁሉ ልቡ እው​ነ​ተኛ ናትና ከተ​ሠ​ራ​ለት ሕግ ሁሉ አል​ወ​ጣም።

25 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም፥ “በም​ድር ላይ ያለው ሁሉ ከሰው ጀምሮ እስከ እን​ስ​ሳና አራ​ዊት፥ እስከ አዕ​ዋ​ፍና በም​ድር ላይ እስ​ከ​ሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀ​ሰው ድረስ ይጥፉ” አለ።

26 ከጥ​ፋት ውኃም ያድ​ነው ዘንድ ኖኅን ለእ​ርሱ መር​ከ​ብን እን​ዲ​ሠራ አዘ​ዘው።

27 ኖኅም ዓመ​ታት በሚ​ቈ​ጠ​ሩ​በት በሁ​ለ​ተ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ዓመት እን​ዳ​ዘ​ዘው ሁሉ መር​ከ​ብን ሠራ።

28 በስ​ድ​ስ​ተ​ኛ​ውም ዓመት በሁ​ለ​ተ​ኛው ወር እስከ ዐሥራ ስድ​ስ​ተ​ኛው ቀን ድረስ እርሱ ገባ። ያገ​ባ​ን​ለ​ትም ሁሉ ወደ መር​ከብ ገባ።

29 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በዐ​ሥራ ሰባ​ተ​ኛው ቀን ማታ መር​ከ​ቡን በውጭ ዘጋው፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሰባ​ቱን የሰ​ማይ ሻሻ​ቴና ሰፊ የሆነ የጥ​ል​ቁን ምን​ጮች አፍ በሰ​ባት ስቍ​ረት ከፈተ።

30 ሻሻ​ቴ​ዎ​ችም ከሰ​ማይ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ዝና​ብን ያወ​ርዱ ዘንድ ጀመሩ።

31 የጥ​ል​ቁም ምን​ጮች ዓለሙ ሁሉ ውኃን እስ​ኪ​ሞላ ድረስ ውኃ​ዎ​ችን ያወጡ ነበር፤ ውኃ​ዎ​ችም በም​ድር ላይ በዙ፤ ውኃ​ውም በረ​ጅሙ ተራራ ሁሉ ላይ ዐሥራ አም​ስት ክንድ ከፍ ከፍ አለ።

32 ውኃ​ዎ​ችም ከፍ ከፍ አሉ። መር​ከ​ቢ​ቱም በም​ድር ላይ ከፍ ከፍ አለች። በው​ኃ​ውም ላይ ትመ​ላ​ለስ ነበር፤ ውኃ​ዎ​ችም በም​ድር ላይ አም​ስት ወር ማለት መቶ አምሳ ቀን ቈዩ። መር​ከ​ቢ​ቱም ሄደች፥ ከአ​ራ​ራት ተራ​ራ​ዎ​ችም በአ​ንዱ ሉባር በሚ​ባል ተራራ ራስ ላይ ዐረ​ፈች።

33 በአ​ራ​ተ​ኛ​ውም ወር ሰፊ የሆነ የጥ​ልቁ ምን​ጮች ተገቱ። የሰ​ማ​ዩም ሻሻቴ ተገታ።

34 በሰ​ባ​ተ​ኛ​ውም ወር መባቻ የም​ድሩ ጥልቅ አፍ ሁሉ ተከ​ፈተ። ውኃ​ዎ​ችም ወደ ታች​ኛ​ዪቱ ጥልቅ ይወ​ርዱ ጀመር።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች