Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ኩፋሌ 5 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በዚ​ያ​ችም ቀን አዳም ከኤ​ዶም ገነት ሲወጣ ለበጎ መዓዛ ነጭ ዕጣን፥ ቀን​ዓ​ትና ልባ​ንጃ፥ ስን​ቡ​ልም ኀፍ​ረ​ቱን በሸ​ፈ​ነ​በት ቀን በጥ​ዋት ፀሓይ ሲወጣ ዐጠነ።

2 በዚ​ያ​ችም ቀን የአ​ራ​ዊ​ትና የእ​ን​ስ​ሳት ሁሉ፥ የሚ​መ​ላ​ለ​ሰ​ውና የሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀ​ሰው፥ የወ​ፎ​ችም ሁሉ አፍ ከመ​ና​ገር ተከ​ለ​ከለ። ከዚያ አስ​ቀ​ድሞ አንዱ ከአ​ንዱ ጋር በአ​ንድ አነ​ጋ​ገ​ርና በአ​ንድ ቋንቋ ይና​ገሩ ነበ​ርና።

3 በኤ​ዶም ገነት የነ​በ​ረ​ው​ንም ሥጋዊ ሁሉ ከኤ​ዶም ገነት አሰ​ና​በተ።

4 ሥጋ ለባሹ ሁሉም በየ​ወ​ገ​ና​ቸ​ውና በየ​ተ​ፈ​ጥ​ሮ​አ​ቸው ወደ ተፈ​ጠ​ረ​ላ​ቸው ቦታ ተበ​ተኑ።

5 ለአ​ዳም ብቻ ከአ​ራ​ዊ​ትና ከእ​ን​ስ​ሳት ሁሉ ተለ​ይቶ፥ ኀፍ​ረ​ቱን ይሸ​ፍን ዘንድ ልብ​ስን ሰጠው። ስለ​ዚህ የሕ​ግን ፍርድ በሚ​ያ​ውቁ ሰዎች ሁሉ ላይ ኀፍ​ረ​ታ​ቸ​ውን እን​ዲ​ሰ​ውሩ እንጂ፥ አሕ​ዛ​ብም እን​ደ​ሚ​ገ​ለጡ እን​ዳ​ይ​ገ​ለጡ በሰ​ማይ ጽላት ታዘዘ።

6 በአ​ራ​ተ​ኛው ወር መባቻ አዳ​ምና ሚስቱ ከኤ​ዶም ገነት ወጥ​ተው በተ​ፈ​ጠ​ሩ​ባት ምድር በኤ​ልዳ ምድር ኖሩ። አዳ​ምም የሚ​ስ​ቱን ስም ሔዋን አላት፤ እስከ መጀ​መ​ሪ​ያው ኢዮ​ቤ​ል​ዩም ድረስ ልጅ አል​ነ​በ​ራ​ቸ​ውም።

7 ከዚ​ህም በኋላ በግ​ብር ዐወ​ቃት፤ እርሱ ግን በኤ​ዶም ገነት እንደ ተማረ ምድ​ርን ያር​ሳት ነበር።

8 በሦ​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ በሁ​ለ​ተ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ ቃየ​ንን ወለ​ደች፤ በአ​ራ​ተ​ኛ​ውም ሱባዔ አቤ​ልን ወለ​ደ​ችው፤ በአ​ም​ስ​ተ​ኛ​ውም ሱባዔ ልጅ​ዋን አዋ​ንን ወለ​ደ​ቻት።

9 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከአ​ቤል እጅ መሥ​ዋ​ዕ​ትን ተቀ​ብ​ሎ​አ​ልና፥ ከቃ​የን እጅ ግን መሥ​ዋ​ትን አል​ተ​ቀ​በ​ለ​ምና በሦ​ስ​ተ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ መጀ​መ​ሪያ ቃየን አቤ​ልን ገደ​ለው፤ በም​ድረ በዳም ገደ​ለው፤ ስለ ተገ​ደ​ለም እየ​ተ​ካ​ሰሰ ደሙ ከም​ድር እስከ ሰማይ ጮኸ።

10 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ስለ ገደ​ለው ስለ አቤል ቃየ​ንን ዘለ​ፈው፤ ስለ ወን​ድሙ ስለ አቤል ደም በም​ድር ላይ ተቅ​በ​ዝ​ባዥ አደ​ረ​ገው፥ በም​ድ​ርም ረገ​መው።

11 ስለ​ዚህ ወን​ድ​ሙን በተ​ን​ኰል የሚ​ገ​ድል ሰው የተ​ረ​ገመ እንደ ሆነ በሰ​ማይ ጽላት ተጻፈ። ያዩም ሁሉ ይሁን አሉ። አይ​ቶም ያል​ተ​ና​ገረ ሰው እንደ እርሱ የተ​ረ​ገመ ይሁን።

12 ስለ​ዚ​ህም እኛ በሰ​ማ​ይና በም​ድር፥ በብ​ር​ሃ​ንና በጨ​ለማ በሁ​ሉም የሚ​ደ​ረ​ገ​ውን ኀጢ​አት ሁሉ በአ​ም​ላ​ካ​ችን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት እን​ና​ገር ዘንድ መጣን አሉ፤ አዳ​ምና ሚስ​ቱም ስለ አቤል አራት የዘ​መን ሱባዔ እያ​ለ​ቀሱ ኖሩ።

13 አዳ​ምም በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ በአ​ራ​ተ​ኛው ዓመት ደስ አለው። ዳግ​መኛ ሚስ​ቱን በግ​ብር ዐወ​ቃት፤ ወንድ ልጅም ወለ​ደ​ች​ለት። “ቃየን ስለ ገደ​ለው ስለ አቤ​ልም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በም​ድር ሌላ ዘር አስ​ነ​ሥ​ቶ​ል​ናል” ብሎ​አ​ልና ስሙን ሴት አለው።

14 በስ​ድ​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ ልጁን አዙ​ራን ወለ​ዳት፥ ቃየ​ንም እኅቱ አዋ​ንን ሚስት ትሆ​ነው ዘንድ አገ​ባት፤ በአ​ራ​ተ​ኛ​ውም ኢዮ​ቤ​ልዩ መጨ​ረሻ ኤኖ​ሕን ወለ​ደ​ች​ለት።

15 በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ሱባዔ በአ​ን​ደ​ኛው ዓመት በም​ድር ቤቶች ተሠሩ። ቃየ​ንም ከተማ ሠራ፤ ስም​ዋ​ንም በልጁ በኤ​ኖሕ ስም ጠራት።

16 አዳ​ምም ሚስቱ ሔዋ​ንን በግ​ብር ዐወ​ቃት። ዳግ​መ​ኛም ዘጠኝ ልጆ​ችን ወለ​ደ​ች​ለት።

17 ሴትም በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ እኅ​ቱን አዙ​ራን ሚስት አድ​ርጎ አገ​ባት።

18 በአ​ራ​ተ​ኛ​ውም ዓመት ሄኖ​ስን ወለ​ደ​ች​ለት። እር​ሱም በም​ድር ላይ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ስም መጥ​ራት የጀ​መረ ነው።

19 በሰ​ባ​ተ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ በሦ​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ ሄኖስ ሚስት ትሆ​ነው ዘንድ እኅቱ ኖአ​ምን አገባ፤ በአ​ም​ስ​ተ​ኛ​ውም ሱባዔ በሦ​ስ​ተ​ኛው ዓመት ወንድ ልጅ ወለ​ደ​ች​ለት፤ ስሙ​ንም ቃይ​ናን አለው።

20 በስ​ም​ን​ተ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ መጨ​ረሻ ቃይ​ናን እኅ​ቱን ሙአ​ሊ​ሊ​ትን ሚስት አድ​ርጎ አገ​ባት፤ በዘ​ጠ​ነ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ሱባዔ በዚ​ህም ሱባዔ በሦ​ስ​ተ​ኛው ዓመት ወንድ ልጅን ወለ​ደ​ች​ለት፤ ስሙ​ንም መላ​ል​ኤል አለው።

21 በዐ​ሥ​ረ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ በሁ​ለ​ተ​ኛው ሱባዔ መላ​ል​ኤል ሚስት ትሆ​ነው ዘንድ የአ​ባ​ቱን ወን​ድም የበ​ራ​ኪ​ሄ​ልን ልጅ ዲናን አገባ። በሦ​ስ​ተ​ኛ​ውም ሱባዔ በስ​ድ​ስ​ተ​ኛው ዓመት ወንድ ልጅን ወለ​ደ​ች​ለት፥ ስሙ​ንም ያሮድ አለው። በዘ​መኑ ትጉ​ሃን የተ​ባሉ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መላ​እ​ክት በም​ድር የሰው ልጆ​ችን ያስ​ተ​ምሩ ዘንድ፥ በም​ድ​ርም ፍር​ድ​ንና ቅን​ነ​ትን ያደ​ርጉ ዘንድ ወደ ምድር ወር​ደ​ዋ​ልና።

22 ያሮ​ድም በዐ​ሥራ አን​ደ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ ሚስት አገባ፤ ስም​ዋም ባረካ ይባ​ላል፤ ይህ​ች​ውም የአ​ባቱ እኅት የራ​ሱ​የል ልጅ ናት፤ በዚ​ህም ኢዮ​ቤ​ልዩ በአ​ራ​ተ​ኛው ሱባዔ ሚስት አገባ፥ በዚህ ኢዮ​ቤ​ልዩ በአ​ራ​ተ​ኛው ዓመት በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ ወንድ ልጅን ወለ​ደ​ች​ለት፤ ስሙ​ንም ሄኖክ አለው፤ እር​ሱም አስ​ቀ​ድሞ በም​ድር ላይ ከተ​ወ​ለዱ ሰዎች ይልቅ መጽ​ሐ​ፍ​ንና ትም​ህ​ር​ትን ጥበ​ብ​ንም ተማረ።

23 ሰዎች በየ​ወ​ራ​ቸው እንደ ሥር​ዐ​ታ​ቸው የዘ​መ​ና​ትን ጊዜ ያውቁ ዘንድ እንደ ወራ​ቸው ሥር​ዐት የሰ​ማ​ይን ምል​ክት በመ​ጽ​ሐፍ ጻፈ።

24 እር​ሱም አስ​ቀ​ድሞ ምስ​ክ​ርን ጻፈ። ለሰው ልጆ​ችም በየ​ወ​ገ​ና​ቸው አሰ​ማ​ባ​ቸው፤ እር​ሱም በሱ​ባዔ የሚ​ቈ​ጠሩ ቍጥ​ሮ​ችን ተና​ገረ፤ የዘ​መ​ኖ​ች​ንም ቀኖች እርሱ ተና​ገረ፤ ወሮ​ች​ንም ሠራ፤ እኛም እንደ ነገ​ር​ነው ዘመ​ኖ​ችን የሚ​ቈ​ጥ​ሩ​ባ​ቸው ሱባ​ዔ​ዎ​ችን ተና​ገረ። የተ​ደ​ረ​ገ​ው​ንና ገና የሚ​ደ​ረ​ገ​ው​ንም ቍርጥ ፍርድ እስ​ከ​ሚ​ደ​ረ​ግ​በት ቀን ድረስ በዘ​መ​ና​ቸው በሰው ልጆች ላይ የሆ​ነ​ው​ንና የሚ​ሆ​ነ​ውን ሌሊት በራ​እይ አየ፤ ዐወ​ቀም።

25 ለም​ስ​ክ​ር​ነ​ትም ጻፈው። በሰው ልጆ​ችም ሁሉ ላይ በየ​ት​ው​ል​ዳ​ቸው በም​ድር ምስ​ክር ሊሆን አኖ​ረው።

26 በዐ​ሥራ ሁለ​ተ​ኛ​ውም ኢዮ​ቤ​ልዩ በሰ​ባ​ተ​ኛው ሱባዔ ሚስት አገባ። ስም​ዋም አድኒ ይባ​ላል፥ ይህ​ች​ውም የዳ​ን​ኤል ልጅ የአ​ባቱ እኅት ልጅ ናት፤ ለእ​ር​ሱም ሚስት ልት​ሆ​ነው አገ​ባት።

27 በዚ​ህም ሱባዔ በስ​ድ​ስ​ተ​ኛው ዓመት ወንድ ልጅን ወለ​ደ​ች​ለት። ስሙ​ንም ማቱ​ሳላ ብሎ ጠራው።

28 ከዚ​ህም በኋላ ከአ​ም​ላክ መላ​እ​ክት ጋር ስድ​ስት የኢ​ዮ​ቤ​ላት ዘመ​ኖ​ችን ኖረ። በም​ድ​ርም ያለ​ውን ሁሉ፥ በሰ​ማ​ይም ያለ​ውን የፀ​ሓ​ይን ሥል​ጣን አሳ​ዩት።

29 ሁሉ​ንም ጻፈ። ከሰው ልጆች ጋር በኀ​ጢ​አት አንድ ሆነው በደል በሠ​ሩት በት​ጉ​ሃ​ንም አዳ​ኘ​ባ​ቸው። እነ​ዚህ ከሰው ልጆች ጋር ይረ​ክሱ ዘንድ፥ በግ​ብ​ርም አንድ ይሆኑ ዘንድ ጀም​ረ​ዋ​ልና፤ ሄኖ​ክም በሁሉ ላይ አዳ​ኘ​ባ​ቸው።

30 ከሰው ልጆ​ችም መካ​ከል ተወ​ሰደ። ለጌ​ት​ነ​ትና ለክ​ብ​ርም ወደ ኤዶም ገነት ወሰ​ድ​ነው፤ እነሆ፥ እርሱ በዚያ የዘ​ለ​ዓ​ለም ቅጣ​ት​ንና ቍርጥ ፍር​ድን፥ የአ​ዳ​ም​ንም ልጆች ኀጢ​አት ሁሉ ይጽ​ፋል።

31 ለሰው ሁሉ ልጅ ያሰማ ዘንድ፥ ቍርጥ ፍር​ድም እስ​ከ​ሚ​ደ​ረ​ግ​ባት ቀን ድረስ የሰ​ውን ሁሉ ሥራ ይና​ገር ዘንድ እርሱ ለም​ል​ክት ተሰ​ጥ​ቶ​አ​ልና ስለ እርሱ በኤ​ዶም ምድር ላይ ሁሉ የጥ​ፋት ውኃን አመጣ።

32 እር​ሱም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ቀ​በ​ለ​ውን ዕጣን በሠ​ርክ አስ​ቀ​ድሞ ዕጣን በሚ​ቃ​ጠ​ል​በት በተ​ቀ​ደ​ሰው ተራራ ላይ ዐጠነ፤ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በም​ድር አራት ቦታ​ዎች አሉ​ትና፥ እነ​ዚ​ህም የኤ​ዶም ገነ​ትና ደብረ ዘይት፥ ይህም ዛሬ አንተ በው​ስጡ ያለ​ህ​በት ደብረ ሲናና ምድ​ርን ለማ​ን​ጻት በሚ​ደ​ረግ በአ​ዲስ ፍጥ​ረት የሚ​ነጻ ደብ​ረ​ጽ​ዮን ናቸው።

33 ስለ​ዚ​ህም ምድር ከበ​ደ​ልና ከር​ኵ​ሰት ሁሉ ለልጅ ልጅ ዘመን ትነ​ጻ​ለች።

34 በዐ​ሥራ አራ​ተ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ ማቱ​ሳላ ሚስ​ቱን አድ​ናን አገባ፤ ይህ​ች​ውም የአ​ባቱ እኅት ልጅ የአ​ዝ​ራ​ኤል ልጅ ናት።

35 በስ​ድ​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ በአ​ን​ደ​ኛው ዘመን ልጅን ወለደ። ስሙ​ንም ላሜህ አለው።

36 በዐ​ሥራ አም​ስ​ተ​ኛው ኢዮ​ቤ​ልዩ በሦ​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ ላሜህ ሚስት አገባ፤ ስም​ዋም ቤቴ​ናስ ይባ​ላል፥ ይህ​ች​ውም የአ​ባቱ የእ​ኅት ልጅ የበ​ራ​ኪ​ኤም ልጅ ናት፤ ሚስት ትሆ​ነው ዘን​ድም አገ​ባት።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች