Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ኩፋሌ 4 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በሁ​ለ​ተ​ኛዉ ሱባዔ በስ​ድ​ስቱ ቀናት በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል አራ​ዊ​ትን ሁሉ፥ እን​ስ​ሳ​ትን ሁሉ፥ አዕ​ዋ​ፍን ሁሉና በም​ድር የሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀ​ሰ​ውን ፍጥ​ረት ሁሉ፥ በው​ኃ​ውም ውስጥ የሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀ​ሰ​ውን ፍጥ​ረት ሁሉ በየ​ወ​ገ​ና​ቸ​ውና በየ​መ​ል​ካ​ቸው ወደ አዳም አመ​ጣን።

2 በመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ዪቱ ቀን አራ​ዊ​ትን፥ በሁ​ለ​ተ​ኛ​ዪቱ ቀን እን​ስ​ሳ​ትን፥ በሦ​ስ​ተ​ኛ​ዪቱ ቀን አዕ​ዋ​ፍን፥ በአ​ራ​ተ​ኛ​ዪቱ ቀን በም​ድር ላይ የሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀ​ሰ​ውን ሁሉ፥ በአ​ም​ስ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ቀን በውኃ ውስጥ የሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀ​ሰ​ውን ሁሉ። አዳ​ምም ሁሉን በየ​ስ​ማ​ቸው ጠራ​ቸው፤ ስማ​ቸ​ውም አዳም እንደ ጠራ​ቸው እን​ዲሁ ሆነ።

3 በእ​ነ​ዚ​ህም በአ​ም​ስቱ ቀኖች አዳም እነ​ዚ​ህን ሁሉ፥ በም​ድር ያለ​ው​ንም ፍጥ​ረት ሁሉ ሴትና ወንድ ሆነው ያይ ነበር። እርሱ ግን ብቻ​ውን ነበረ። እንደ እርሱ ያለ ረዳ​ት​ንም ለራሱ አላ​ገ​ኘም ነበር።

4 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ለእኛ እን​ዲህ አለን፥ “አዳም ብቻ​ውን ይኖር ዘንድ መል​ካም አይ​ደ​ለም፤ ነገር ግን እንደ እርሱ ያለ ረዳ​ትን እን​ፍ​ጠ​ር​ለት።” አም​ላ​ካ​ችን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በእ​ርሱ ላይ እን​ቅ​ል​ፍን አመ​ጣ​በት፤ እር​ሱም ተኛ።

5 ከአ​ጥ​ን​ቶ​ቹም መካ​ከል አንድ አጥ​ንት ወስዶ ሴትን ፈጠ​ራት። ይህ​ችም ጎን ከአ​ጥ​ን​ቶች መካ​ከል የሴት መገኛ ናት፤ ስለ እር​ስ​ዋም ፋንታ ሥጋን ሞላ። ሴትም አድ​ርጎ ፈጠ​ራት። አዳ​ም​ንም ከእ​ን​ቅ​ልፉ አነ​ቃው።

6 አዳ​ምም በስ​ድ​ስ​ተ​ኛ​ዪቱ ቀን ከእ​ን​ቅ​ልፉ ነቅቶ በተ​ነሣ ጊዜ ወደ እርሱ አመ​ጣት፥ ዐወ​ቃ​ትም። እር​ሱም፥ “ከእኔ ከባ​ልዋ ተገ​ኝ​ታ​ለ​ችና ይህች አጥ​ንት ከአ​ጥ​ንቴ፥ ሥጋም ከሥ​ጋዬ ናት፤ እር​ስ​ዋም ሚስት ትሁ​ነኝ” አላት። ስለ​ዚህ ባልና ሚስት አንድ አካል ይሆ​ናሉ።

7 ስለ​ዚ​ህም ሰው አባ​ቱ​ንና እና​ቱን ይተ​ዋል፤ ከሚ​ስ​ቱም ጋር አንድ ይሆ​ናል፥ አንድ አካ​ልም ይሆ​ናሉ።

8 በመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ዪቱ ሱባዔ አዳም ተፈ​ጠረ፤ ሚስ​ቱም የተ​ገ​ኘ​ች​በት ጎኑ ተፈ​ጠረ፤ በሁ​ለ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ሱባዔ እር​ስ​ዋን አሳ​የው፤ ስለ​ዚ​ህም በሕ​ርስ ጊዜ ለወ​ንድ ልጅ አንድ ሱባዔ፥ ለሴት ልጅ ሁለት ሱባዔ የመ​ጠ​በቅ ትእ​ዛዝ ተሰጠ።

9 በተ​ፈ​ጠ​ረ​ባ​ትም ምድር ለአ​ዳም አርባ ቀን ከተ​ፈ​ጸ​መ​ለት በኋላ ያበ​ጃ​ትና ይጠ​ብ​ቃት ዘንድ ወደ ኤዶም ገነት አስ​ገ​ባ​ነው። ሚስ​ቱ​ንም በሰ​ማ​ን​ያ​ኛው ቀን አስ​ገ​ባ​ናት።

10 ከዚ​ህም በኋላ ወደ ኤዶም ገነት ገባች፤ ስለ​ዚህ ለም​ት​ወ​ልድ ሴት በጽ​ላተ ሰማይ ሥር​ዐት ተጻፈ። ወንድ ልጅ ብት​ወ​ልድ እንደ መጀ​መ​ሪ​ያው ሰባት ቀን በአ​ራ​ስ​ነቷ ሰባት ቀን ትቈ​ያ​ለች፥ ሠላሳ ሦስት ቀንም በመ​ን​ጻቷ ደም ትቈ​ያ​ለች።

11 የተ​ቀ​ደ​ሰ​ውን ሁሉ አት​ንካ፤ ለወ​ንድ ልጅ የታ​ዘ​ዘ​ውን ይህን ቀን እስ​ክ​ት​ፈ​ጽም ድረስ ወደ ቤተ መቅ​ደስ አት​ግባ። ሴት ልጅ ብት​ወ​ልድ እንደ መጀ​መ​ሪ​ያ​ዎቹ ሁለት ሱባ​ዔ​ያት በአ​ራ​ስ​ነቷ ሁለት ሱባ​ዔ​ያት ትቈ​ያ​ለች። ስድሳ ስድ​ስት ቀንም በመ​ን​ጻቷ ደም ትቈ​ያ​ለች። ሁሉም ሰማ​ንያ ቀኖች ይሆ​ናሉ።

12 እነ​ዚ​ህ​ንም ሰማ​ንያ ቀኖች ከፈ​ጸ​መች በኋላ ገነት ከም​ድር ሁሉ የተ​ቀ​ደ​ሰች ናትና፥ በው​ስ​ጥ​ዋም የበ​ቀ​ለው እን​ጨት ሁሉ የተ​ቀ​ደሰ ነውና ወደ ኤዶም ገነት አገ​ባ​ናት።

13 ስለ​ዚ​ህም ወንድ ልጅና ሴት ልጅ ለም​ት​ወ​ልድ ሴት የእ​ነ​ዚህ ቀኖች ሥር​ዐት ተሠራ፤ ለወ​ንድ ልጅና ለሴት ልጅ የታ​ዘዙ እነ​ዚህ ቀኖች እስ​ኪ​ፈ​ጸሙ የተ​ቀ​ደ​ሰ​ውን ሁሉ አት​ንካ፤ ወደ መቅ​ደ​ስም ሁሉ አት​ግባ። እስ​ራ​ኤ​ልም በዘ​መኑ ሁሉ ይጠ​ብ​ቁት ዘንድ የተ​ጻ​ፈው ሕግና ሥር​ዐት ይህ ነው።

14 በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ኢዮ​ቤ​ልዩ በመ​ጀ​መ​ሪያ ሱባዔ አዳ​ምና ሚስቱ በኤ​ዶም ገነት ሰባት ዓመት ሲሠ​ሩና ሕጉን ሲጠ​ብቁ ኖሩ። ሥራ​ንም ሰጠ​ነው፤ ለማ​ገ​ል​ገ​ልም ተገ​ልጦ የሚ​ታ​የ​ውን ሥራ ሁሉ እያ​ስ​ተ​ማ​ር​ነው ኖርን፤ እር​ሱም እየ​ሠራ ኖረ።

15 እርሱ ግን ዕራ​ቁ​ቱን ነበረ፤ ዕራ​ቁ​ቱ​ንም እንደ ሆነ አያ​ው​ቅም ነበር፥ አያ​ር​ፍ​ምም ነበር። ተክ​ል​ንም ከወ​ፎ​ችና ከአ​ራ​ዊት፥ ከእ​ን​ስ​ሳ​ትም ይጠ​ብቅ ነበር።

16 ፍሬ​ው​ንም ለቅሞ ይበላ ነበር፥ የተ​ረ​ፈ​ው​ንም ለእ​ር​ሱና ለሚ​ስቱ ያኖር ነበር፤ የሚ​ጠ​ብ​ቀ​ው​ንም ያኖር ነበር፤ ሰባ​ቱን ዓመት ጠን​ቅቆ ቈጥሮ በዚያ የፈ​ጸ​ማ​ቸው የሰ​ባቱ ዓመት ፍጻሜ ባለቀ ጊዜ፥

17 በሁ​ለ​ተ​ኛው ወር በዐ​ሥራ ሰባ​ተ​ኛው ቀን እባብ መጥቶ ወደ ሔዋን ቀረበ። እባ​ቡም ሔዋ​ንን፥ “በገ​ነት ካሉ ዛፎች ፍሬ ሁሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፦ ከእ​ርሱ አት​ብሉ ብሎ አዝ​ዞ​አ​ች​ኋ​ልን?” አላት።

18 እር​ስ​ዋም እን​ዲህ አለ​ችው፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር፦ በገ​ነት ካለ ዛፍ ፍሬ ሁሉ ብሉ፥ በገ​ነት መካ​ከል ካለ ዛፍ ፍሬ ግን አት​ብሉ፥ እን​ዳ​ት​ሞ​ቱም አት​ንኩ” አለን።

19 እባ​ብም ሔዋ​ንን፥ “ከእ​ርሱ በም​ት​በ​ሉ​በት ቀን ዐይ​ኖ​ቻ​ችሁ እን​ደ​ሚ​በሩ፥ አማ​ል​ክ​ትም እን​ደ​ም​ት​ሆኑ፥ ክፉ​ው​ንና በጎ​ው​ንም እን​ደ​ም​ታ​ውቁ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያው​ቃ​ልና ነው እንጂ ሞትን የም​ት​ሞቱ አይ​ደ​ለም” አላት።

20 ሔዋ​ንም ዛፉ ያማረ እንደ ሆነ፥ ለማ​የ​ትም ደስ የሚ​ያ​ሰኝ፥ ፍሬ​ውም ለመ​ብ​ላት የሚ​ያ​ስ​ጐ​መጅ እንደ ሆነ ባየች ጊዜ ከእ​ርሱ ወስዳ በላች። ኀፍ​ረ​ቷ​ንም በቀ​ደ​መው በበ​ለሱ ቅጠል ሸፈ​ነች። ለአ​ዳ​ምም ሰጠ​ች​ውና በላ። ዐይ​ኖ​ቹም አዩ፤ ዕራ​ቁ​ቱ​ንም እንደ ሆነ ባየ ጊዜ የበ​ለስ ቅጠል ወስዶ ሰፋ፤ ግል​ድም አድ​ር​ጎም ኀፍ​ረ​ቱን ሸፈነ።

21 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እባ​ቡን ረገ​መው፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ምም ፈረ​ደ​በት።

22 ሔዋ​ን​ንም የእ​ባ​ቡን ቃል ሰምታ በል​ታ​ለ​ችና ፈረ​ደ​ባት፤ “ኀዘ​ን​ሽ​ንና ጣር​ሽን ፈጽሜ አበ​ዛ​ዋ​ለሁ፤ በኀ​ዘን ልጆ​ችን ውለጂ፥ መመ​ለ​ሻ​ሽም ወደ ባልሽ ይሁን፤ እር​ሱም ይግ​ዛሽ” አላት።

23 አዳ​ም​ንም፥ “የሚ​ስ​ት​ህን ቃል ሰም​ተህ ከእ​ርሱ እን​ዳ​ት​በላ ካዘ​ዝ​ሁህ ከዚያ ዛፍ በል​ተ​ሃ​ልና በአ​ንተ ምክ​ን​ያት ምድር የተ​ረ​ገ​መች ትሁን፤ እሾ​ህና አሜ​ከላ ይብ​ቀ​ል​ብህ፤ አንተ ከም​ድር ተገ​ኝ​ተ​ሃ​ልና ወደ ምድ​ርም ትመ​ለ​ሳ​ለ​ህና ከእ​ር​ስዋ ወደ ተገ​ኘ​ህ​ባት ወደ ምድር እስ​ክ​ት​መ​ለስ ድረስ በፊ​ትህ ወዝ እን​ጀ​ራ​ህን ብላ” አለው።

24 የቍ​ር​በት ልብ​ስ​ንም አደ​ረ​ገ​ላ​ቸው፤ አለ​በ​ሳ​ቸ​ውም ከኤ​ዶም ገነ​ትም አሰ​ና​በ​ታ​ቸው።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች