Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ኩፋሌ 3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ከዚ​ህም ሁሉ በኋላ ሰውን ፈጠረ፤ ወን​ድና ሴት አድ​ርጎ ፈጠ​ራ​ቸው፤ በም​ድር ላይና በባ​ሕር ውስጥ ባለ​ውም ሁሉ ላይ አሠ​ለ​ጠ​ነው። በሚ​በ​ርሩ አዕ​ዋፍ ላይና በአ​ራ​ዊት ላይ፥ በእ​ን​ስ​ሳት ላይና በም​ድር ላይ በሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀ​ሰው ላይ፥ በም​ድ​ርም ሁሉ ላይ፥ በዚ​ህም ሁሉ ላይ አሠ​ለ​ጠ​ነው፤ በስ​ድ​ስ​ተ​ኛ​ዪቱ ቀን እነ​ዚ​ህን አራት ዓይ​ነት ፍጥ​ረ​ታት ፈጠረ።

2 ሁሉም ሃያ ሁለት ዓይ​ነት ፍጥ​ረት ሆነ፤ በስ​ድ​ስ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ቀን በሰ​ማ​ይና በም​ድር፥ በባ​ሕ​ሩና በጥ​ልቁ ውስጥ፥ በብ​ር​ሃ​ንና በጨ​ለማ መካ​ከል፥ በሁ​ሉም ላይ ያለ​ውን ፍጥ​ረት ሁሉ ፈጥሮ ፈጸመ።

3 ስድ​ስት ቀን ሥራ ሠር​ተን በሰ​ባ​ተ​ኛ​ዪቱ ቀን ከሥራ ሁሉ እና​ርፍ ዘንድ ታላቅ ምል​ክት ሰባ​ተ​ኛ​ዪ​ቱን ቀን ሰጠን።

4 መላ​እ​ክተ ገጽ ሁሉና የም​ስ​ጋና መላ​እ​ክት ሁሉ እነ​ዚህ ሁለቱ ታላ​ላቅ ወገ​ኖች ናቸው። ከእ​ር​ሱም ጋር በሰ​ማ​ይና በም​ድር ይህን እና​ከ​ብር ዘንድ አዘ​ዘን።

5 እን​ዲ​ህም አለን፥ “እነሆ፥ እኔ ከአ​ሕ​ዛብ መካ​ከል ሕዝ​ብን እለ​ያ​ለሁ፤ እነ​ር​ሱም ሰን​በ​ትን ያከ​ብ​ራሉ። ለእ​ኔም ሕዝብ አድ​ርጌ እለ​ያ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ የሰ​ን​በ​ት​ንም ቀን እንደ ቀደ​ስ​ኋት እባ​ር​ካ​ቸ​ዋ​ለሁ። ለእ​ኔም እለ​ያ​ቸ​ዋ​ለሁ።

6 እን​ዲ​ህም እባ​ር​ካ​ቸ​ዋ​ለሁ። ሕዝ​ቤም ይሆ​ናሉ፤ እኔም አም​ላክ እሆ​ና​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በሁ​ሉም ካየ​ሁት የያ​ዕ​ቆ​ብን ዘር መረ​ጥሁ፥ ለእ​ኔም የበ​ኵር ልጅ አድ​ርጌ ጻፍ​ሁት፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለ​ምም ቀደ​ስ​ሁት።

7 “ከሥራ ሁሉ ያር​ፉ​ባት ዘንድ የሰ​ን​በ​ታ​ትን ቀን አመ​ለ​ክ​ታ​ቸ​ዋ​ለሁ። እን​ደ​ዚ​ሁም በዓል ያከ​ብ​ሩ​ባት ዘንድ ምል​ክት አደ​ረ​ግ​ሁ​ባት።

8 እነ​ር​ሱም በሰ​ባ​ተ​ኛ​ዪቱ ቀን ለመ​ብ​ላ​ትና ለመ​ጠ​ጣት፥ ሁሉን የፈ​ጠረ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ለማ​መ​ስ​ገን ከእኛ ጋር ነበሩ። ከእኛ ጋርም በአ​ን​ድ​ነት ያርፉ ዘንድ ከአ​ሕ​ዛብ ሁሉ ተለ​ይቶ የሚ​ታይ ሕዝ​ብን ባረከ፥ ቀደ​ሰም።

9 በዘ​መኑ ሁሉ በፊቱ የሚ​ቀ​በ​ለው በጎ መዓዛ ያርግ ዘንድ በፊቱ መሥ​ዋ​ዕ​ትን ሠዋ፥ ከአ​ዳም ጀምሮ እስከ ያዕ​ቆብ ድረስ ያሉ አበው ሃያ ሁለት ናቸው። እስከ ሰባ​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ቀን ድረስ ሃያ ሁለት ዓይ​ነት ፍጥ​ረት ተፈ​ጠረ። ይህም የተ​ባ​ረ​ከና የተ​ቀ​ደሰ ሰን​በቱ ነው። እር​ሱም ቡሩ​ክና ቅዱስ ነው።

10 ይህም ከዚህ ጋር ለም​ስ​ጋ​ናና ለበ​ረ​ከት ሆነ። ቀድሞ ሰባ​ተ​ኛው ቀን እንደ ተቀ​ደ​ሰና እንደ ተባ​ረከ በዘ​መኑ ሁሉ ለም​ስ​ክ​ሩና ለሕጉ የተ​ባ​ረ​ኩና የተ​ቀ​ደሱ ይሆኑ ዘንድ ይህ ለእ​ርሱ ተሰ​ጠው።

11 “በመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ዪቱ ሱባዔ ሰማ​ይ​ንና ምድ​ርን፥ በስ​ድ​ስት ቀን የተ​ፈ​ጠ​ረ​ው​ንም ፍጥ​ረት ሁሉ ፈጠረ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ለፍ​ጥ​ረቱ ሁሉ የተ​ቀ​ደ​ሰች የበ​ዓል ቀንን ሰጠ። ስለ​ዚ​ህም ሥራን ሁሉ የሚ​ሠ​ራ​ባት ሁሉ ይሞት ዘንድ፥ የሚ​ሽ​ራ​ትም ሞትን ይሞት ዘንድ አዘዘ።

12 አን​ተም የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች እዘ​ዛ​ቸው፥ እነ​ር​ሱም እን​ዲ​ያ​ከ​ብ​ሯት፥ ሥራ​ንም ሁሉ እን​ዳ​ይ​ሠ​ሩ​ባት፥ እን​ዳ​ይ​ሽ​ሩ​አ​ትም፥ ያችን ዕለት ይጠ​ብቁ፤ ከዕ​ለ​ታት ሁሉ እር​ስዋ የተ​ቀ​ደ​ሰች ናትና።

13 የሚ​ያ​ረ​ክ​ሳ​ትም ሁሉ ሞትን ይሙት፤ ሥራ​ንም የሚ​ሠ​ራ​ባት ሁሉ ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ ሞትን ይሙት። የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ከም​ድር እን​ዳ​ይ​ጠፉ በት​ው​ል​ዳ​ቸው ይህ​ችን ቀን ይጠ​ብቁ። የተ​ባ​ረ​ከ​ችና የተ​ቀ​ደ​ሰች ናትና።

14 የሚ​ጠ​ብ​ቃት ሰው ሁሉ፥ ከሥ​ራ​ውም ሁሉ የሚ​ያ​ር​ፍ​ባት ሰው በዘ​መኑ ሁሉ እንደ እኛ የተ​ቀ​ደ​ሰና የተ​ባ​ረከ ይሆ​ናል።

15 “ለእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች፦ የዚ​ህ​ችን ቀን ፍርድ አስ​ረ​ድ​ተህ ንገር፤ ያክ​ብ​ሯ​ትም፤ የማ​ይ​ገባ ሥራን ለመ​ሥ​ራ​ትም የተ​ዘ​ጋጁ እን​ዳ​ይ​ሆኑ በል​ቡ​ና​ቸው ስሕ​ተት አይ​ተ​ዉ​አት፤ የሚ​ታ​የ​ውን ፈቃ​ዳ​ቸ​ው​ንም በእ​ር​ስዋ ለማ​ድ​ረግ የሚ​በ​ላ​ው​ንና የሚ​ጠ​ጣ​ውን ሁሉ ያዘ​ጋ​ጁ​ባት ዘንድ፥

16 ውኃ​ንም ለመ​ቅ​ዳት፥ በአ​ደ​ባ​ባ​ያ​ቸ​ውም ሸክ​ሙን ሁሉ ለማ​ግ​ባ​ትና ለማ​ው​ጣት፥ እነ​ርሱ በስ​ድ​ስት ቀን በቤ​ታ​ቸው ያላ​ዘ​ጋ​ጁ​ትን ሥራ አይ​ሥሩ።

17 በኢ​ዮ​ቤ​ልዩ ከሚ​ቈ​ጠር ቀን ሁሉ ተለ​ይታ የከ​በ​ረች ናትና በዚ​ህች ቀን ከቤት ወደ ቤት አያ​ው​ጡ​ባት፥ አያ​ግ​ቡ​ባ​ትም። በም​ድር ዕረ​ፍት ያደ​ር​ጉ​ባት ዘንድ ለሥ​ጋዊ ሁሉ ሳይ​ታ​ወቅ እኛ በሰ​ማ​ያት ዕረ​ፍ​ትን አደ​ረ​ግ​ን​ባት።”

18 የሁሉ ፈጣ​ሪም ባረ​ካት፤ ከእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ብቻ በቀር በእ​ር​ስዋ ዕረ​ፍት ለማ​ድ​ረግ አሕ​ዛ​ብን ሁሉ አል​መ​ረ​ጠም፤ ነገር ግን በል​ቶና ጠጥቶ በም​ድር ዕረ​ፍ​ትን ሊያ​ደ​ር​ግ​ባት ለእ​ርሱ ብቻ ሰጠው።

19 ከቀኑ ሁሉ ተለ​ይታ ለበ​ረ​ከ​ትና ለቅ​ድ​ስና ለማ​መ​ስ​ገ​ኛም ልት​ሆን ይህ​ችን ቀን የፈ​ጠረ የሁሉ ፈጣሪ ባረ​ካት፤ ይህ ሕግ፥ ይህም ምስ​ክር ለእ​ስ​ራ​ኤል ልጆ​ችና ለት​ው​ል​ዳ​ቸ​ውም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ሥር​ዐት ሆኖ ተሰጠ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች