Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ኩፋሌ 12 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ከዚህ ነገር በኋላ በዚህ ሱባዔ በአ​ራ​ተ​ኛው ዓመት በሦ​ስ​ተ​ኛው ወር መባቻ፥ “አብ​ራም፥ አት​ፍራ፤ ጠበ​ቃህ እኔ ነኝ፤ ዋጋ​ህም እጅግ ይበ​ዛል፥” ሲል የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል በሕ​ልም ወደ አብ​ራም መጣ።

2 እር​ሱም እን​ዲህ አለ፥ “አቤቱ፥ ምን ትሰ​ጠ​ኛ​ለህ? እኔ ልጅ ሳል​ወ​ልድ እሄ​ዳ​ለሁ፤ የደ​ማ​ስቆ ሰው የሚ​ሆን የአ​ማ​ቲ​የል ልጅ የማ​ሴቅ ልጅ ኤል​ኤ​ዘር እርሱ ይወ​ር​ሰ​ኛል፤ ለእኔ ግን ልጅ አል​ሰ​ጠ​ኸ​ኝም፤ ልጅ ስጠኝ።”

3 እር​ሱም፥ “ከአ​ብ​ራ​ክህ የሚ​ወ​ለድ ልጅ እርሱ ይወ​ር​ስ​ሃል እንጂ ይህ አይ​ወ​ር​ስ​ህም” አለው።

4 ወደ ውጭም አው​ጥቶ፥ “ወደ ሰማይ ተመ​ል​ከት፤ መቍ​ጠር ይቻ​ልህ እንደ ሆነ ከዋ​ክ​ብ​ትን ቍጠር” አለው። ሰማ​ይን አየ፤ ከዋ​ክ​ብ​ት​ንም ተመ​ለ​ከተ፤ እር​ሱም፥ “ዘርህ እን​ደ​ዚህ ይሆ​ናል” አለው። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም አመ​ነው፤ ጽድቅ ሆኖም ተቈ​ጠ​ረ​ለት።

5 “ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይዘ​ሃት ልት​ኖር ለአ​ን​ተም ከአ​ን​ተም በኋላ ለል​ጆ​ችህ ልት​ሆን የከ​ነ​ዓ​ና​ው​ያ​ንን ሀገር እሰ​ጥህ ዘንድ የከ​ላ​ው​ዴ​ዎን ዕጣ ከም​ት​ሆን ከዑር ያወ​ጣ​ሁህ አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እኔ ነኝ” አለው።

6 እር​ሱም፥ “አቤቱ አቤቱ፥ እን​ደ​ም​ወ​ር​ሳት በምን አው​ቃ​ለሁ?” አለ።

7 እር​ሱም፥ “የሦ​ስት ዓመት ወይ​ፈን፥ የሦ​ስት ዓመት ፍየል፥ የሦ​ስት ዓመት በግ፥ ዋኖ​ስና ርግ​ብ​ንም አም​ጣ​ልኝ” አለው።

8 ይህ​ንም ሁሉ በወር እኩ​ሌታ አመጣ። እርሱ ግን የኬ​ብ​ሮን አቅ​ራ​ቢያ በም​ት​ሆን በመ​ምሬ ባለ ግራር ሥር ተቀ​ምጦ ነበር።

9 በዚ​ያም መሠ​ዊ​ያን ሠራ፥ ይህ​ንም ሁሉ ሠዋ፤ በመ​ሠ​ዊ​ያ​ውም ላይ ደማ​ቸ​ውን አፈ​ሰሰ፤ ከሁ​ለት ከሁ​ለ​ትም አደ​ረ​ጋ​ቸው፤ በየ​መ​ል​ካ​ቸ​ውም በአ​ን​ጻ​ራ​ቸው አኖ​ራ​ቸው፤ አዕ​ዋ​ፍን ግን ጨርሶ አል​ቈ​ረ​ጣ​ቸ​ውም። ወፎ​ችም ወደ መሥ​ዋ​ዕቱ ይወ​ርዱ ነበር።

10 አብ​ራም ግን ይከ​ለ​ክ​ላ​ቸው ነበር፤ ወፎ​ችም ይበ​ሉ​አ​ቸው ዘንድ አል​ተ​ወም ነበር።

11 ፀሐ​ይም በገባ ጊዜ እን​ዲህ ሆነ፥ በአ​ብ​ራም እን​ቅ​ልፍ መጣ​በት ፤ እነ​ሆም፥ የሚ​ያ​ስ​ፈራ ጽኑ ጨለማ በላዩ ወደ​ቀ​በት።

12 ለአ​ብ​ራ​ምም እን​ዲህ ተብሎ ተነ​ገረ፥ “ዘርህ በአ​ሕ​ዛብ ሀገር ስደ​ተ​ኞች እን​ደ​ሚ​ሆኑ፥ አራት መቶ ዓመ​ትም እን​ደ​ሚ​ገ​ዙ​አ​ቸ​ውና መከራ እን​ደ​ሚ​ያ​ጸ​ኑ​ባ​ቸው ፈጽ​መህ ዕወቅ፤ የሚ​ገ​ዙ​አ​ቸ​ው​ንም ወገ​ኖች እኔ እፈ​ር​ድ​ባ​ቸ​ዋ​ለሁ።

13 ከዚህ በኋላ ከብዙ ገን​ዘብ ጋር ከዚያ ይወ​ጣሉ። አን​ተም ወደ አባ​ቶ​ችህ በሰ​ላም ትሄ​ዳ​ለህ፤ በበጎ እር​ግ​ናም ትቀ​በ​ራ​ለህ።

14 በአ​ራ​ተ​ኛው ትው​ልድ ወደ​ዚህ ይመ​ለ​ሳሉ፤ እስከ ዛሬ ድረስ የአ​ሞ​ራ​ው​ያን ኀጢ​አት አል​ተ​ፈ​ጸ​መ​ምና።”

15 ከእ​ን​ቅ​ል​ፉም ነቅቶ ተነሣ፤ ፀሐ​ይም ገባ፤ እሳ​ትም ይነድ ጀመር፤ እነሆ፥ ምድ​ጃው እየ​ጤሰ የእ​ሳቱ ነበ​ል​ባል በመ​ሠ​ዊ​ያው መካ​ከል አለፈ።

16 በዚ​ያ​ችም ሌሊት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከአ​ብ​ራም ጋር እን​ዲህ ሲል ቃል ኪዳን አደ​ረገ፥ “ከግ​ብፅ ወንዝ ጀምሮ እስከ ታላቁ ወንዝ፤ እስከ ኤፍ​ራ​ጥስ ወንዝ ድረስ፥ ይህ​ችን ሀገር ለል​ጆ​ችህ እሰ​ጣ​ለሁ፤ የቄ​ኔ​ዎ​ስ​ንና የቄ​ኔ​ዜ​ዎ​ስን፥ የቀ​ድ​ሞ​ኔ​ዎ​ስን፥ የፌ​ር​ዜ​ዎ​ስ​ንና የራ​ፋ​ይ​ምን፥ የፌ​ኮ​ሬ​ዎ​ስን፥ የኤ​ዌ​ዎ​ስ​ንና የአ​ሞ​ሬ​ዎ​ስን፥ የከ​ና​ኔ​ዎ​ስ​ንና የጌ​ር​ጌ​ሴ​ዎ​ስን፥ የኢ​ያ​ቡ​ሴ​ዎ​ስ​ንም ሀገር እሰ​ጥ​ሀ​ለሁ።”

17 አብ​ራ​ምም ሄዶ መሠ​ዊ​ያ​ውን አዘ​ጋጀ፤ አዕ​ዋ​ፍ​ንና መሥ​ዋ​ዕ​ታ​ቸ​ውን፥ ወይ​ና​ቸ​ው​ንም አቀ​ረበ፤ እሳ​ትም በላው።

18 በዚ​ያ​ችም ወር ከኖኅ ጋር ቃል ኪዳን እንደ አደ​ረ​ግን በዚ​ችም ዕለት ከአ​ብ​ራም ጋር ቃል ኪዳን አደ​ረ​ግን።

19 አብ​ራ​ምም ይህ​ችን በዓ​ልና ሥር​ዐ​ቷ​ንም እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ ለራሱ አጸ​ናት፤ አብ​ራ​ምም ደስ አለው፤ ይህ​ንም ነገር ሁሉ ለሚ​ስቱ ለሶራ ነገ​ራት፤ ልጅ እን​ደ​ሚ​ወ​ለ​ድ​ለ​ትም አመነ። እር​ስዋ ግን ልጅ አት​ወ​ል​ድም ነበር፤ ሶራም ባል​ዋን አብ​ራ​ምን መከ​ረ​ችው፦ “ከእ​ር​ስዋ የሚ​ወ​ለ​ደ​ውን ልጅ አሳ​ድ​ግ​ል​ሃ​ለ​ሁና ወደ ግብ​ፃ​ዊቱ አገ​ል​ጋዬ ወደ አጋር ግባ” አለ​ችው።

20 አብ​ራ​ምም የሚ​ስቱ የሶ​ራን ቃል ሰማ፥ “እን​ዳ​ልሽ አድ​ርጊ” አላት። ሶራም ግብ​ፃ​ዊት አገ​ል​ጋ​ይ​ዋን አጋ​ርን አም​ጥታ ሚስት ትሆ​ነው ዘንድ ለባ​ልዋ ለአ​ብ​ር​ሃም ሰጠ​ቻት።

21 ወደ እር​ስ​ዋም ገባ፥ ፀነ​ሰች፥ ወንድ ልጅ​ንም ወለ​ደች። በዚህ ሱባዔ በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ዓመት ስሙን ይስ​ማ​ኤል ብሎ ጠራው። በዚ​ያም ዓመት የአ​ብ​ራም ዕድሜ ሰማ​ንያ ስድ​ስት ዓመት ነበር።

22 በዚህ ኢዮ​ቤ​ልዩ በአ​ራ​ተ​ኛው ሱባዔ በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ዓመት በሦ​ስ​ተ​ኛው ወር በወሩ እኩ​ሌታ መጀ​መ​ሪያ ስለ ደረ​ሰው የስ​ንዴ አዝ​መራ አብ​ራም በዓ​ልን አደ​ረገ።

23 በመ​ሠ​ዊ​ያ​ውም ላይ የእ​ህ​ሉን መጀ​መ​ሪያ አዲስ መሥ​ዋ​ዕት አድ​ርጎ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አቀ​ረበ፤ ወይ​ፈ​ኑ​ንና የበ​ጉን ሙክት፥ በጉ​ንም በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ የሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕት አድ​ርጎ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አቀ​ረበ። መሥ​ዋ​ዕ​ታ​ቸ​ው​ንና ወይ​ና​ቸ​ው​ንም ከነጭ ዕጣን ጋር አቀ​ረበ።

24 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ለአ​ብ​ራም ተገ​ለ​ጠ​ለት፤ እን​ዲ​ህም አለው፥ “ሁሉን ቻይ አም​ላክ እኔ ነኝ። በፊቴ የም​ት​ወ​ደድ ሁን፤ ፍጹ​ምም ሁን፤ በእ​ኔና በአ​ንተ መካ​ከ​ልም ቃል ኪዳን እሰ​ጣ​ለሁ፤ እጅ​ግም አከ​ብ​ር​ሃ​ለሁ።”

25 አብ​ራ​ምም በግ​ን​ባሩ ወደቀ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ዲህ ብሎ ተና​ገ​ረው፥ “እነሆ፥ ሥር​ዐቴ ከአ​ንተ ጋር ነው፤ ለብዙ አሕ​ዛ​ብም አባት አደ​ር​ግ​ሃ​ለሁ።

26 እን​ግ​ዲህ ወዲህ ስምህ አብ​ራም አይ​ባል፤ የብዙ ሕዝብ አባት አድ​ር​ጌ​ሃ​ለ​ሁና ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ ስምህ አብ​ር​ሃም ይባል። አን​ተ​ንም በአ​ሕ​ዛብ መካ​ከል ፈጽሜ አከ​ብ​ር​ሃ​ለሁ፤ ነገ​ሥ​ታ​ቱም ከአ​ንተ ይወ​ለ​ዳሉ።

27 በእ​ኔና በአ​ንተ መካ​ከል፥ ከአ​ን​ተም በኋላ በል​ጆ​ችህ መካ​ከል በወ​ገ​ና​ቸው የዘ​ለ​ዓ​ለም ሥር​ዐት ልት​ሆን፥ ቃል ኪዳ​ኔን አጸ​ና​ለሁ፤ ለአ​ን​ተና ከአ​ን​ተም በኋላ ለዘ​ርህ አም​ላክ እሆን ዘንድ ለዘ​ለ​ዓ​ለም በም​ት​ገ​ዛት፥ ተሰ​ደህ በሄ​ድ​ህ​ባት በከ​ነ​ዓን ቃል ኪዳ​ኔን አጸ​ና​ለሁ፤ አም​ላ​ካ​ቸ​ውም እሆ​ና​ቸ​ዋ​ለሁ።”

28 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አብ​ር​ሃ​ምን እን​ዲህ አለው፥ “አንተ ቃል ኪዳ​ኔን ጠብቅ፤ ከአ​ን​ተም በኋላ ልጆ​ችህ ይጠ​ብቁ፤ ወን​ዶች ልጆ​ቻ​ች​ሁን ሁሉ ትገ​ዝ​ራ​ላ​ችሁ፤ የሰ​ው​ነ​ታ​ች​ሁ​ንም ሸን​ኮፍ ሁሉ ትገ​ዝ​ራ​ላ​ችሁ፤ በእ​ኔና በእ​ና​ንተ መካ​ከ​ልም ለልጅ ልጅ ለዘ​ለ​ዓ​ለም የኪ​ዳኔ ምል​ክት ይሆ​ናል።

29 በስ​ም​ን​ተ​ኛ​ውም ቀን ወንድ ልጅን ሁሉ በየ​ወ​ገ​ና​ችሁ ትገ​ዝ​ራ​ላ​ችሁ። በቤት የተ​ወ​ለ​ደው፥ ከአ​ሕ​ዛ​ብም ልጆች ሁሉ በወ​ርቅ የገ​ዛ​ች​ሁት፥ ከዘ​ር​ህም ያይ​ደለ ቢሆን ይገ​ዘሩ፤ በቤ​ትህ የተ​ወ​ለ​ደም፥ በወ​ር​ቅ​ህም የገ​ዛ​ኸው ቢሆን ይገ​ዘሩ።

30 ለዘ​ለ​ዓ​ለም ሥር​ዐቴ ሊሆን ቃል ኪዳኔ በሰ​ው​ነ​ታ​ችሁ ጸንቶ ይኖ​ራል። ግዙር ያል​ሆነ ወንድ ልጃ​ችሁ ሁሉ፥ በስ​ም​ን​ተ​ኛ​ዪ​ቱም ቀን የሰ​ው​ነ​ቱን ሰን​ኮፍ ያል​ተ​ገ​ዘረ ሁሉ ቃል ኪዳ​ኔን አፍ​ር​ሶ​አ​ልና ያ ሰው ከወ​ገኑ ተለ​ይቶ ይጥፋ።”

31 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አብ​ር​ሃ​ምን እን​ዲህ አለው፥ “ሚስ​ትህ ሶራ ስምዋ ሳራ ነውና ከእ​ን​ግ​ዲህ ወዲያ ስምዋ ሶራ ተብሎ አይ​ጠራ፤ እባ​ር​ካ​ታ​ለሁ፤ ከእ​ር​ስ​ዋም ልጅ እሰ​ጥ​ሃ​ለሁ፤ እር​ሱ​ንም እባ​ር​ከ​ዋ​ለሁ፤ ታላቅ ወገ​ንም ይሆ​ናል፤ የአ​ሕ​ዛብ ነገ​ሥ​ታ​ትም ከእ​ርሱ ይወ​ለ​ዳሉ።”

32 አብ​ር​ሃ​ምም በግ​ን​ባሩ ወደቀ። ደስ ብሎ​ትም በልቡ እን​ዲህ አለ፥ “በመቶ ዘመኔ ልጅ እወ​ል​ዳ​ለ​ሁን? ዘጠና ዓመት የሆ​ናት ሳራስ ልጅ ትወ​ል​ዳ​ለ​ችን?”

33 አብ​ር​ሃ​ምም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እን​ዲህ አለው፥ “ይስ​ማ​ኤል በፊ​ትህ ቢኖር በወ​ደ​ድሁ ነበር።”

34 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አለው፥ “ይሁን፥ ሳራም ወንድ ልጅን ትወ​ል​ድ​ል​ሃ​ለች፤ ስሙ​ንም ይስ​ሐቅ ብለህ ትጠ​ራ​ዋ​ለህ፤ ቃል ኪዳ​ኔ​ንም የዘ​ለ​ዓ​ለም ቃል ኪዳን ሊሆን ከእ​ርሱ ጋር አጸ​ና​ለሁ፤ ከእ​ር​ሱም በኋላ ለል​ጆቹ አጸ​ና​ለሁ።

35 ስለ ይስ​ማ​ኤ​ልም ሰማ​ሁህ፤ እነሆ፥ እባ​ር​ከ​ዋ​ለሁ፥ አገ​ነ​ዋ​ለሁ፤ እጅ​ግም አበ​ዛ​ዋ​ለሁ፤ ዐሥራ ሁለት መሳ​ፍ​ን​ት​ንም ይወ​ል​ዳል፤ በታ​ላ​ቅም ሕዝብ ላይ እሾ​መ​ዋ​ለሁ።

36 ቃል ኪዳ​ኔን ግን በዚህ ወራት በሁ​ለ​ተ​ኛው ዓመት ሳራ ከም​ት​ወ​ል​ድ​ልህ ከይ​ስ​ሐቅ ጋር አጸ​ና​ለሁ።” ከእ​ር​ሱም ጋር ይህን ተና​ግሮ ከጨ​ረሰ በኋላ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አብ​ር​ሃም ካለ​በት ወጣ።

37 አብ​ር​ሃ​ምም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዳ​ለው አደ​ረገ፤ ልጁ ይስ​ማ​ኤ​ል​ንና በቤት የተ​ወ​ለ​ደ​ውን ሁሉ፥ በወ​ርቁ የገ​ዛ​ው​ንም፥ በቤ​ቱም ያለ ወንድ ልጅን ሁሉ ወስዶ የሰ​ው​ነ​ታ​ቸ​ውን ሰን​ኮፍ ገረዘ።

38 በዚ​ህ​ችም ቀን አብ​ር​ሃም ተገ​ረዘ፤ ቤተ ሰቦ​ቹም፥ በወ​ርቅ የገ​ዛ​ቸ​ውም ሁሉ፥ ከአ​ሕ​ዛ​ብም የተ​ወ​ለዱ ሁሉ ከእ​ርሱ ጋር ተገ​ረዙ። ይህም ሕግ ለልጅ ልጅ ሁሉ የዘ​ለ​ዓ​ለም ነው።

39 ይህ የዘ​ለ​ዓ​ለም ሥር​ዐት ነውና፥ በሰ​ማይ ጽላ​ትም ተጽ​ፎ​አ​ልና ቀን ማሳ​ጠር የለም፤ ከስ​ም​ንቱ ቀንም አን​ዲት ቀን መተ​ላ​ለፍ የለም።

40 እስከ ስም​ንት ቀንም ድረስ የሰ​ው​ነ​ቱን ሰን​ኮፍ ያል​ተ​ገ​ረዘ ሰው ሁሉ ከጥ​ፋት ልጆች ወገን ነውና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለአ​ብ​ር​ሃም ከገ​ባው ቃል ኪዳን ልጆች ወገን አይ​ደ​ለም።

41 ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይሆን ዘንድ ምል​ክት የለ​ውም፤ የአ​ም​ላ​ካ​ችን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ኪዳን ስላ​ፈ​ረሰ ከም​ድር ለመ​ጥ​ፋ​ትና ለመ​ደ​ም​ሰስ፥ ከም​ድ​ርም ለመ​ነ​ቀል የተ​ገባ ነውና። መላ​እ​ክተ ገጽ ሁሉና የም​ስ​ጋና መላ​እ​ክት ሁሉ ከተ​ፈ​ጠ​ሩ​በት ቀን ጀምሮ ተፈ​ጥ​ሮ​አ​ቸው እን​ዲህ ነውና።

42 በመ​ላ​እ​ክተ ገጽና በም​ስ​ጋና መላ​እ​ክት አን​ጻር ከእ​ርሱ ጋርና ከቅ​ዱ​ሳን መላ​እ​ክት ጋር ይሆኑ ዘንድ እስ​ራ​ኤ​ልን ቀደ​ሰው።

43 አን​ተም የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች እዘዝ፤ የዚ​ህን ቃል ኪዳ​ኔ​ንም ምል​ክት ይጠ​ብቁ፤ ለል​ጆ​ቻ​ቸ​ውም የዘ​ለ​ዓ​ለም ሥር​ዐት ይሁን፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለም በእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ሁሉ ላይ ይጠ​ብ​ቁት ዘንድ ለቃል ኪዳን ሥር​ዐት ሠር​ቶ​አ​ልና ከም​ድር እን​ዳ​ይ​ጠፉ ይሁኑ። ይስ​ማ​ኤ​ል​ንና ልጆ​ቹን፥ ወን​ድ​ሞ​ቹ​ንና ዔሳ​ው​ንም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ወደ እርሱ አላ​ቀ​ረ​ባ​ቸ​ውም፤ ምንም የአ​ብ​ር​ሃም ልጆች ቢሆ​ኑና ቢወ​ድ​ዳ​ቸ​ውም እነ​ር​ሱን አል​መ​ረ​ጠም።

44 ሕዝብ ይሆ​ኑት ዘንድ እስ​ራ​ኤ​ልን ለይቶ መረጠ። ብዙ አሕ​ዛ​ብና፥ ብዙ ሕዝብ ሁሉ የእ​ርሱ ናቸ​ውና፥ ሁሉም ለእ​ርሱ ይገ​ባ​ልና ከሰው ልጆች ሁሉ ለይቶ ሰበ​ሰ​በው። ነገር ግን ከእ​ርሱ በኋላ ያስ​ቱ​አ​ቸው ዘንድ መና​ፍ​ስ​ትን በሁሉ ላይ አሠ​ለ​ጠነ።

45 በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ ግን ገዢ​አ​ቸው እርሱ ብቻ ነውና፥ መል​አ​ክም ቢሆን መን​ፈ​ስም ቢሆን ማን​ንም አላ​ሠ​ለ​ጠ​ነም። እር​ሱም ይጠ​ብ​ቃ​ቸ​ዋል። ከመ​ላ​እ​ክ​ትና ከመ​ና​ፍ​ስት እጅ፥ ከሥ​ል​ጣ​ና​ትም ሁሉ እጅ ይጠ​ብ​ቃ​ቸው ዘንድ ይመ​ራ​መ​ራ​ቸ​ዋል። እነ​ርሱ ልጆቹ ይሆ​ኑት ዘንድ እር​ሱም ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ አም​ላክ ይሆ​ና​ቸው ዘንድ ይባ​ር​ካ​ቸ​ዋል።

46 አሁ​ንም የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ይህ​ችን ሥር​ዐት ሐሰት እን​ደ​ሚ​ያ​ደ​ርጉ እኔ እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ። በሰ​ው​ነ​ታ​ቸው ከመ​ገ​ረ​ዛ​ቸው የተ​ነሣ ልጆ​ቻ​ቸ​ውን ሳይ​ገ​ርዙ ይቀ​ራ​ሉና፤ የቤ​ል​ሆ​ርም ልጆች ሁሉ ልጆ​ቻ​ቸ​ውን እንደ ተወ​ለዱ ሳይ​ገ​ርዙ ይተ​ዋሉ።

47 ቃል ኪዳ​ኑን አፍ​ር​ሰ​ዋ​ልና፥ ከቃ​ሉም ወጥ​ተ​ዋ​ልና ያች ጽኑ መዓት ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ታዝዛ በእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ትደ​ረ​ጋ​ለች። የዚ​ህ​ንም ምል​ክት ሥር​ዐ​ቱን እን​ዳ​ል​ፈ​ጸሙ ከም​ድር ፈጽሞ ለመ​ጥ​ፋት ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውን እንደ አሕ​ዛብ አድ​ር​ገ​ዋ​ልና ተበ​ሳ​ጭ​ተው ተሳ​ደቡ።

48 በዚ​ችም ምድር ለሚ​ሠ​ራው ስሕ​ተት፥ ኀጢ​አ​ትም ሁሉ ፈጽሞ ይሰ​ረይ ዘንድ እን​ግ​ዲህ ወዲህ የኀ​ጢ​አት ስር​የ​ትና ይቅ​ርታ የላ​ቸ​ውም።

49 በአ​ራ​ተ​ኛው ወር መባቻ በመ​ምሬ ባለው በግ​ራሩ ሥር ለአ​ብ​ር​ሃም ተገ​ለ​ጥ​ን​ለት፤ ከእ​ር​ሱም ጋር ተነ​ጋ​ገ​ርን። ከሚ​ስቱ ከሳ​ራም ልጅ እን​ደ​ሚ​ሰ​ጠው ነገ​ር​ነው፤ ሳራም ይህን ነገር ከአ​ብ​ር​ሃም ጋር እንደ ተነ​ጋ​ገ​ርን ሰም​ታ​ለ​ችና ሳቀች። እኛም ዘለ​ፍ​ናት፤ እር​ስ​ዋም ፈርታ ስለ ተነ​ገ​ረው ነገር እንደ ሳቀች አስ​ተ​ባ​በ​ለች።

50 የል​ጅ​ዋ​ንም ስም ስሙ ይስ​ሐቅ ተብሎ በሰ​ማይ ጽላት እንደ ተሠ​ራና እንደ ተጻፈ ነገ​ር​ናት። ያን​ጊ​ዜም ወደ እር​ስዋ በተ​መ​ለ​ስን ጊዜ እር​ስዋ ወንድ ልጅን ፀነ​ሰች።

51 በዚ​ያም ወር እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በገ​ሞ​ራና በሰ​ዶም፥ በሰ​ቡ​ኢ​ምና በዮ​ር​ዳ​ኖስ አው​ራጃ ሁሉ ፍር​ዱን አደ​ረገ። በእ​ሳ​ትና በድኝ አቃ​ጠ​ላ​ቸው፤ እጅግ ክፉ​ዎ​ችና ኀጢ​አ​ተ​ኞች እንደ ሆኑ በሰ​ው​ነ​ታ​ቸ​ውም እየ​ሴ​ሰኑ እን​ደ​ሚ​ረ​ክሱ፥ በም​ድር ላይም ርኵ​ሰ​ትን እን​ደ​ሚ​ሠሩ፥ እነሆ፥ ሥራ​ቸ​ውን ሁሉ እንደ ነገ​ር​ሁህ እስ​ከ​ዚ​ህች ቀን ድረስ አጠ​ፋ​ቸው።

52 እን​ደ​ዚ​ሁም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሰዶም ርኵ​ሰት በሠ​ሩ​ባ​ቸው ቦታ​ዎች ሁሉ እንደ ሰዶም ፍርድ ያደ​ር​ጋል።

53 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አብ​ር​ሃ​ምን አስ​ቦ​ታ​ልና ሎጥን አዳ​ነው፤ ከጥ​ፋ​ትም መካ​ከል አወ​ጣው። ከአ​ዳም ዘመን ጀምሮ እስ​ከ​ዚያ ቀን ድረስ በም​ድር ላይ ያል​ተ​ደ​ረገ ኀጢ​አ​ትን እርሱ ከል​ጆቹ ጋር በም​ድር አደ​ረገ፤ አባት ከልጁ ጋር ተኝ​ቶ​አ​ልና።

54 ያጠ​ፋ​ቸ​ውና ይነ​ቅ​ላ​ቸው፥ ቅጣ​ታ​ቸ​ው​ንም እንደ ሰዶም ቅጣት ያደ​ርግ ዘንድ፥ በፍ​ርድ ቀንም በም​ድር የሰ​ውን ዘር ሁሉ እን​ዳ​ያ​ስ​ቀ​ር​ለት፥ እነሆ፥ ታዘዘ። በል​ጆ​ቹም ሁሉ ላይ በሰ​ማይ ጽላት ተቀ​ረፀ።

55 በዚ​ህም ወር አብ​ር​ሃም ከኬ​ብ​ሮን ተጕዞ ሄዶ በጌ​ራ​ሮን ተራ​ሮች ባሉ በቃ​ዴ​ስና በሱር መካ​ከል ተቀ​መጠ።

56 በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ወር እኩ​ሌ​ታም ከዚያ ተጕዞ በመ​ሐላ ጕድ​ጓድ አጠ​ገብ ተቀ​መጠ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች