Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ኩፋሌ 11 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 አብ​ራም በሕ​ይ​ወት በኖ​ረ​በት በስ​ድ​ሳ​ኛው ዓመት፥ ይኸ​ውም በአ​ራ​ተ​ኛው ሱባኤ በአ​ራ​ተ​ኛው ዓመት፥ አብ​ራም ሌሊት ተነ​ሥቶ የጣ​ዖ​ታ​ቱን ቤት አቃ​ጠለ። በቤት ያለ​ው​ንም ዕቃ ሁሉ አቃ​ጠለ። ያወቀ ሰው ግን አል​ነ​በ​ረም።

2 በሌ​ሊ​ትም ተነ​ሥ​ተው ጣዖ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ከእ​ሳት ውስጥ ያወጡ ዘንድ ወደዱ።

3 አራ​ንም ያድ​ና​ቸው ዘንድ ተወ​ረ​ወረ፤ በላ​ዩም እሳት ነደ​ደ​በት፤ በእ​ሳ​ትም ተቃ​ጥሎ የከ​ላ​ው​ዴ​ዎን ዕጣ በም​ት​ሆን በዑር በአ​ባቱ በታራ ፊት ሞተ። የከ​ላ​ው​ዴ​ዎን ዕጣ በም​ት​ሆን በዑ​ርም ቀበ​ሩት።

4 ታራም የከ​ላ​ው​ዴ​ዎን ዕጣ ከም​ት​ሆን ከዑር ወጣ። እር​ሱና ልጆቹ ወደ ሊባ​ኖስ ምድ​ርና ወደ ከነ​ዓን ምድር፥ ወደ ካራ​ንም ምድር ይመጡ ዘንድ ወጣ።

5 አብ​ራ​ምም ከአ​ባቱ ጋር በካ​ራን ሁለት የዓ​መ​ቶች ሱባዔ ተቀ​መጠ።

6 በስ​ድ​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ዓመት አብ​ራም ተነሣ፤ በሰ​ባ​ተ​ኛው ወር መባቻ ከማታ እስከ ጥዋት ድረስ ከዋ​ክ​ብ​ትን ይቈ​ጥር ዘን​ድና ስለ ዝናም የዓ​መቱ ጠባይ ምን እን​ደ​ሚ​ሆን ያይ ዘንድ በሌ​ሊት ወጥቶ ተቀ​መጠ።

7 ብቻ​ው​ንም ተቀ​ምጦ ይቈ​ጥር ነበር፥ ቃልም ወደ ልቡ መጣ፤ “የከ​ዋ​ክ​ብት ምል​ክት ሁሉ፥ የፀ​ሐ​ይና የጨ​ረ​ቃም ምል​ክት ሁሉ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እጅ ነው። ጥዋ​ትም ማታም ያዘ​ንብ ዘንድ ቢወድ፥ እን​ዳ​ያ​ዘ​ን​ብም ቢወድ እኔ ለምን እመ​ራ​መ​ራ​ለሁ? ሁሉም በእጁ ነው” አለ።

8 በዚ​ህ​ችም ሌሊት ጸለየ፥ እን​ዲ​ህም አለ፥ “አም​ላኬ አም​ላኬ ሆይ፥ ልዑል አም​ላክ፥ አንተ ብቻ ለእኔ አም​ላክ ነህ፤ አንተ ሁሉን ፈጠ​ርህ፤ የእ​ጅህ ፍጥ​ረት ሁሉ ጸንቶ ይኖ​ራል፤ እኔ አን​ተ​ንና መን​ግ​ሥ​ት​ህን ወደ​ድሁ፤ ከክ​ፉ​ዎች በሰው ልቡና ከሚ​ሠ​ለ​ጥኑ ከመ​ና​ፍ​ስት እጅ አድ​ነኝ፤ አም​ላኬ ሆይ፥ አን​ተን ከመ​ከ​ተል አያ​ስ​ቱኝ፤ እኔ​ንም ዘሬ​ንም ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ ለዘ​ለ​ዓ​ለም እን​ዳ​ን​ስት አድ​ር​ገን።

9 ወደ እነ​ር​ሱም እመ​ለስ ዘንድ ፊቴን ወደ​ሚሹ ወደ ከላ​ው​ዴ​ዎን ዑር ልመ​ለ​ስን? ወይስ በዚህ ቦታ ልቀ​መጥ? ያገ​ለ​ግል ዘንድ በባ​ሪ​ያህ እጅ የቀ​ና​ውን መን​ገድ በፊ​ትህ አቅና። አም​ላኬ ሆይ፥ በል​ቡ​ናዬ ስሕ​ተት አል​ሂድ።”

10 እር​ሱም ይህን ተና​ግ​ሮና ጸልዮ በጨ​ረሰ ጊዜ፥ እነሆ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል በእኔ እጅ እን​ዲህ ሲል ወደ እርሱ ተላከ፥ “አንተ ከሀ​ገ​ርህ፥ ከዘ​መ​ዶ​ች​ህና ከአ​ባ​ትህ ቤት ወጥ​ተህ እኔ ወደ​ማ​ሳ​ይህ ሀገር ሂድ፤ እጅ​ግም ብዙ ወገን አደ​ር​ግ​ሃ​ለሁ፤ እባ​ር​ክ​ህ​ማ​ለሁ፤ ስም​ህ​ንም ከፍ ከፍ አደ​ር​ጋ​ለሁ፤ በም​ድ​ሩም ሁሉ የተ​ባ​ረ​ክህ ትሆ​ና​ለህ።

11 የም​ድር አሕ​ዛ​ብም ሁሉ በአ​ንተ ይባ​ረ​ካሉ፤ የሚ​መ​ር​ቁ​ህን እመ​ር​ቃ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ የሚ​ረ​ግ​ሙ​ህ​ንም እረ​ግ​ማ​ቸ​ዋ​ለሁ። ለአ​ን​ተና ለል​ጆ​ችህ፥ ለልጅ ልጆ​ች​ህም፥ ለዘ​ር​ህም ሁሉ አም​ላክ እሆ​ና​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ከአ​ን​ተም በኋላ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ልጅ ልጅ ዘመን ድረስ አም​ላ​ክህ እኔ ነኝና አት​ፍራ።”

12 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ክም እን​ዲህ አለኝ፥ “ከው​ድ​ቀት ቀን ጀምሮ ከሰው ልጅ ሁሉ ቋንቋ ተለ​ይ​ቶ​አ​ልና የተ​ገ​ለ​ጠች ቋን​ቋን ይሰ​ማና ይና​ገር ዘንድ አፉ​ንና ጆሮ​ውን ክፈት።”

13 እኔም አፉ​ንና ጆሮ​ውን፥ ከን​ፈ​ሩ​ንም ከፈ​ትሁ፤ በት​ው​ልድ ቋን​ቋው በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ ቋን​ቋም ከእ​ርሱ ጋር እና​ገር ጀመ​ርሁ፤ የአ​ባ​ቶ​ቹ​ንም መጽ​ሐፍ ወሰደ፤ እነ​ዚ​ያም በዕ​ብ​ራ​ይ​ስጥ ቋንቋ የተ​ጻፉ ነበሩ። ደግ​ሞም ጻፋ​ቸው፤ ከዚ​ያም ቀን ጀምሮ ይማ​ራ​ቸው ጀመር። የጸ​ነ​ነ​ው​ንም ሁሉ እኔ እነ​ግ​ረው ነበር፤ ዝና​ብም በሚ​ዘ​ን​ብ​ባ​ቸው በስ​ድ​ስቱ ወሮች ተማ​ራ​ቸው።

14 በስ​ድ​ስ​ተ​ኛው ሱባዔ በሰ​ባ​ተ​ኛው ዓመት እን​ዲህ ሆነ፤ ከአ​ባቱ ጋር ተነ​ጋ​ገረ፤ ከካ​ራን ወደ ከነ​ዓን ሄዶ አይ​ቶ​አት ወደ እርሱ ይመ​ለስ ዘንድ እን​ደ​ሚ​ሄድ ነገ​ረው።

15 አባቱ ታራም እን​ዲህ አለው፥ “በሰ​ላም ሂድ፤ የሰ​ላም አም​ላ​ክም ጎዳ​ና​ህን ያቅ​ና​ልህ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከአ​ንተ ጋር ይሁን፤ ከክፉ ሁሉ ይጠ​ብ​ቅህ፤ በሚ​ያ​ዩህ ሰዎች ፊት ቸር​ነ​ት​ንና ይቅ​ር​ታን፥ መወ​ደ​ድ​ንም ይስ​ጥህ፤ በአ​ን​ተም ላይ ክፉ ነገ​ርን ለማ​ድ​ረግ የሰው ልጆች ሁሉ አይ​ሠ​ል​ጥ​ኑ​ብህ፤ በሰ​ላም ሂድ።

16 በእ​ር​ስ​ዋም ለመ​ኖር ለዐ​ይ​ኖ​ችህ ያማ​ረች ምድ​ርን ብታይ፥ መጥ​ተህ ወደ አንተ ውሰ​ደኝ፤ ለአ​ንተ ልጅ ይሆ​ንህ ዘንድ የወ​ን​ድ​ም​ህን የአ​ራን ልጅ ሎጥ​ንም ከአ​ንተ ጋር ውሰ​ደው፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከአ​ንተ ጋር ይሁን፤ በሰ​ላም እስ​ክ​ት​መ​ለ​ስም ድረስ ወን​ድ​ምህ ናኮ​ርን በእኔ ዘንድ ተወው፤ ሁላ​ች​ንም በአ​ን​ድ​ነት ከአ​ንተ ጋር እን​ሄ​ዳ​ለን።”

17 አብ​ራ​ምም ሚስ​ቱን ሶራ​ንና የወ​ን​ድ​ሙን የአ​ራን ልጅ ሎጥን ይዞ ከካ​ራን ወደ ከነ​ዓን ሄደ። ወደ ሱርም መጣ፤ እስከ ሰቂ​ሞ​ንም ድረስ ተመ​ላ​ለሰ፤ በረ​ጅም ግራር ሥር አደረ፤ ከኢ​ማት መግ​ቢያ ጀምሮ ረጅም ግራር እስ​ካ​ለ​በት ድረስ ሀገ​ሪቱ እጅግ ያማ​ረች እንደ ሆነች እነሆ፥ አየ።

18 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም፥ “ለአ​ን​ተና ለል​ጆ​ችህ ይህ​ችን ሀገር እሰ​ጣ​ች​ኋ​ለሁ” አለው። በዚ​ያም መሠ​ዊ​ያን ሠራ፤ ለተ​ገ​ለ​ጠ​ለት ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ የሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕ​ትን አቀ​ረበ።

19 ከዚ​ያም ተነ​ሥቶ በም​ዕ​ራብ አን​ጻር ወዳ​ለች ወደ ቤቴል ተራ​ራና በም​ሥ​ራቅ አን​ጻር ወዳ​ለች ወደ ጋይ ሄደ፤ በዚ​ያም ድን​ኳ​ኑን ተከለ፤ ባያ​ትም ጊዜ፥ እነሆ፥ ሀገ​ሪቱ ሰፊ ነበ​ረች፤ እጅ​ግም ያማ​ረች ነበ​ረች፤ ሁሉም በእ​ር​ስዋ ላይ ይበ​ቅ​ላል፤ ወይን፥ በለስ፥ ሮማን፥ ወይራ፥ ግራር፥ ቡጥን፥ ዘይት፥ ዋንዛ፥ ሰኖ​ባር፥ የሊ​ባ​ኖ​ስም ዛፍ፥ የዱ​ርም ዛፍ ሁሉ የሚ​በ​ቅ​ል​ባት ናት፤ ውኃ​ውም በተ​ራ​ራው ላይ ነበር።

20 የከ​ላ​ው​ዴ​ዎ​ና​ው​ያን ዕጣ ከም​ት​ሆን ከዑር አው​ጥቶ ወደ​ዚህ ተራራ ያመ​ጣ​ውን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም አመ​ሰ​ገ​ነው።

21 በሰ​ባ​ተ​ኛው ሱባዔ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዓመት በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር መባቻ እን​ዲህ ሆነ። በዚያ ተራራ መሠ​ዊ​ያን ሠራ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ስም ጠራ፥ “አንተ አም​ላኬ ሆይ፥ የዘ​ለ​ዓ​ለም አም​ላክ አንተ ነህ” አለ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከእ​ርሱ ጋር ይኖር ዘንድ በሕ​ይ​ወ​ቱም ዘመን ሁሉ እን​ዳ​ይ​ለ​የው በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕ​ትን አቀ​ረበ።

22 ከዚ​ያም ተነ​ሥቶ ወደ ደቡብ ሄደ፤ እስከ ኬብ​ሮ​ንም ደረሰ። ኬብ​ሮ​ንም ያን​ጊዜ ተሠ​ርታ ነበር። በዚ​ያም ሁለት ዓመት ተቀ​መጠ። ሎጥም እስ​ኪ​ገባ ድረስ ወደ ደቡብ ሀገር ሄደ።

23 በም​ድ​ርም ድርቅ ሆነ፤ አብ​ራ​ምም በዚህ ሱባዔ በሦ​ስ​ተ​ኛው ዓመት ወደ ግብፅ ሄደ፤ ሚስቱ ከእ​ርሱ ሳት​ወ​ሰድ በግ​ብፅ አም​ስት ዓመት ኖረ። የግ​ብፅ ክፍል የም​ት​ሆን ጠና​ይ​ስም ያን​ጊዜ ከኬ​ብ​ሮን በኋላ በሰ​ባት ዓመት ተሠ​ርታ ነበር።

24 ፈር​ዖ​ንም የአ​ብ​ራ​ምን ሚስት ሶራን በወ​ሰ​ዳት ጊዜ እን​ዲህ ሆነ፤ ስለ አብ​ራም ሚስት ስለ ሶራ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፈር​ዖ​ንን በደዌ ገረፈ፤ ቤተ ሰቡ​ንም ሁሉ በጽኑ መቅ​ሠ​ፍት ገረፈ።

25 አብ​ራ​ምም በገ​ን​ዘብ፥ በበ​ጎ​ችና በላ​ሞች፥ በአ​ህ​ዮ​ችና በፈ​ረ​ሶች፥ በግ​መ​ሎ​ችም፥ በወ​ን​ዶች ባሪ​ያ​ዎ​ችና በሴ​ቶች ባሪ​ያ​ዎች፥ በብ​ርና በወ​ርቅ እጅግ የከ​በረ ነበረ። የወ​ን​ድሙ ልጅ ሎጥም በገ​ን​ዘብ እንደ እርሱ የከ​በረ ነበረ።

26 ፈር​ዖ​ንም የአ​ብ​ራ​ምን ሚስት ሶራን መለሰ። ከግ​ብ​ፅም ተነ​ሥቶ በቤ​ቴል ምሥ​ራ​ቅና በም​ዕ​ራብ መካ​ከል ወደ አለው ቀድሞ ድን​ኳ​ኑን ተክ​ሎ​በት ወደ ነበ​ረው ወደ ጋይ የመ​ሠ​ዊያ ቦታ ሄደ።

27 በሰ​ላም የመ​ለ​ሰው አም​ላኩ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም አመ​ሰ​ገ​ነው።

28 በአ​ርባ አንድ ኢዮ​ቤ​ልዩ፥ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ሱባዔ በሦ​ስ​ተ​ኛው ዓመት እን​ዲህ ሆነ፤ ወደ​ዚህ ቦታ ተመ​ለሰ፤ በመ​ሠ​ዊ​ያ​ውም ላይ የሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕ​ትን አቀ​ረበ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ስም ጠራ፥ “ልዑል አም​ላክ የም​ት​ሆን አንተ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሆይ፥ ለዘ​ለ​ዓ​ለም አም​ላኬ ነህ” አለ።

29 በዚህ ሱባዔ በአ​ራ​ተ​ኛው ዓመት ሎጥ ከእ​ርሱ ተለየ፤ በሰ​ዶ​ምም ኖረ። የሰ​ዶም ሰዎች ግን እጅግ ኀጢ​አ​ተ​ኞች ነበሩ። የወ​ን​ድ​ሙም ልጅ ከእ​ርሱ ስለ ተለየ በልቡ አዘነ። ሎጥ በተ​ማ​ረ​ከ​በት በዚያ ዓመት ልጅ አል​ነ​በ​ረ​ው​ምና።

30 ሎጥም ከእ​ርሱ ከተ​ለየ በኋላ በዚህ ሱባዔ በአ​ራ​ተ​ኛው ዓመት እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አብ​ራ​ምን አለው፥ “በዚያ ትኖር ዘንድ ካለ​ህ​በት ከዚያ ቦታ ሁነህ ዐይ​ኖ​ች​ህን ወደ ሰሜ​ንና ሊባ፥ ወደ ባሕ​ርና ምሥ​ራቅ አቅና፤ ይህ​ችን የም​ታ​ያ​ትን ሀገር ሁሉ ለአ​ን​ተና ለል​ጆ​ችህ እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ እሰ​ጣ​ች​ኋ​ለ​ሁና።

31 ልጆ​ች​ህ​ንም እንደ ባሕር አሸዋ አደ​ር​ጋ​ለሁ፤ ሰው የባ​ሕር አሸ​ዋን መቍ​ጠር ይችል እንደ ሆነ ልጆ​ች​ህም ይቈ​ጠ​ራሉ፤ ተነ​ሥ​ተህ ቁመ​ቷ​ንና ወር​ድ​ዋን ዙራት፤ ሁሉ​ንም ተመ​ል​ከት፤ ለል​ጆ​ችህ እሰ​ጣ​ታ​ለ​ሁና።”

32 አብ​ራ​ምም ወደ ኬብ​ሮን ሄደ፤ በዚ​ያም ተቀ​መጠ።

33 በዚ​ያም ዓመት የኤ​ላም ንጉሥ ኮሎ​ዶ​ጎ​ሞር መጣ፤ የሰ​ና​ዖ​ርም ንጉሥ አም​ራ​ፌል፥ የሲ​ላ​ሳር ንጉሥ አሪ​ኦክ፥ የአ​ሕ​ዛብ ንጉ​ሥም ቲር​ጋል መጡ፤ የገ​ሞ​ራ​ንም ንጉሥ ወጉት።

34 የሰ​ዶም ንጉሥ ግን ሸሸ፤ በጨው ባሕር በኩል በሲ​ዲም ሸለቆ ብዙ ሰዎች በጦር ቈስ​ለው ወደቁ፤ ሰዶ​ም​ንና አዳ​ማን ሴቦ​ኢ​ም​ንም ማረኩ፤ የአ​ብ​ራ​ምን የወ​ን​ድ​ሙን ልጅ ሎጥ​ንም ማረኩ፤ ገን​ዘ​ቡ​ንም ሁሉ ዘረፉ፤ እስከ ዳንም ድረስ ሄደ። ከጦር ያመ​ለጠ አንድ ሰውም መጥቶ የወ​ን​ድሙ ልጅ ሎጥ እንደ ተማ​ረከ ለአ​ብ​ራም ነገ​ረው። አሽ​ከ​ሮ​ቹ​ንም አስ​ታ​ጠቀ።

35 ከቀ​ዳ​ም​ያት ሁሉ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዐሥ​ራ​ትን እን​ዲ​ሰጡ በአ​ብ​ር​ሃ​ምና በል​ጆቹ ሥር​ዐት ተሠራ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ይይ​ዙት ዘንድ በፊቱ ለሚ​ያ​ገ​ለ​ግሉ ለካ​ህ​ናቱ እን​ዲ​ሰ​ጡ​አ​ቸው የዘ​ለ​ዓ​ለም ሥር​ዐ​ትን ሠራ።

36 ከሁ​ሉም ከእ​ህ​ሉም፥ ከወ​ይ​ኑም፥ ከዘ​ይ​ቱም፥ ከላ​ሞ​ችም፥ ከበ​ጎ​ችም፥ ከፍ​የ​ሎ​ችም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዐሥ​ራት ይሰጡ ዘንድ ለልጅ ልጅ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ሠር​ቶ​ታ​ልና ለዚህ ሕግ የተ​ወ​ሰነ ዘመን የለ​ውም።

37 እር​ሱም በፊት ደስ ብሎ​አ​ቸው ሊበ​ሉ​ትና ሊጠ​ጡት ለካ​ህ​ናት ሰጠ።

38 የሰ​ዶ​ምም ንጉሥ ወደ እርሱ ደረሰ፤ በፊ​ቱም ሰገደ፥ “ጌታ​ችን አብ​ራም ሆይ ፥ ያዳ​ን​ኸ​ውን ሰው ስጠን፤ ምር​ኮው ግን ለአ​ንተ ይሁ​ን​ልህ” አለው።

39 አብ​ራ​ምም፥ “እኔ አብ​ራ​ምን አበ​ለ​ጸ​ግ​ሁት የም​ትል እን​ዳ​ት​ሆን፥ ጐል​ማ​ሶች ከበ​ሉት በቀር ከአ​ንተ ገን​ዘብ ሁሉ የክር ፈት​ልና የጫማ ጠፍር እን​ዳ​ል​ወ​ስድ ገናና ወደ ሆነ አም​ላኬ እኔ እጆ​ችን አነ​ሣ​ለሁ፤ ነገር ግን ከእኔ ጋር የሄዱ ሰዎች አው​ና​ንና ኤሴ​ኬል፥ መም​ሬም እነ​ርሱ ፈን​ታ​ቸ​ውን ይው​ሰዱ” አለው።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች