Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ኢያሱ 15 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ለይ​ሁዳ ነገድ የተ​ሰጠ ርስት

1 የይ​ሁ​ዳም ነገድ ድን​በር በየ​ወ​ገ​ና​ቸው ከኤ​ዶ​ም​ያስ ዳርቻ፥ ከጺን ምድረ በዳ ጀምሮ በዐ​ዜብ በኩል እስከ ቃዴስ ድረስ ነው።

2 በደ​ቡ​ብም በኩል ያለው ድን​በ​ራ​ቸው እስከ ጨው ባሕር ዳርቻ ወደ ሊባ እስ​ከ​ሚ​ወ​ስ​ደው መን​ገድ ነበረ።

3 ከዚ​ያም በአ​ቅ​ረ​ቢን ዐቀ​በት ፊት ይሄ​ዳል፤ ወደ ጺንም ይወ​ጣል፤ በቃ​ዴስ በርኔ ወደ ደቡብ በኩል ይወ​ጣል፤ በአ​ስ​ሮ​ንም በኩል ያል​ፋል፤ ወደ ሰራ​ዳም ይወ​ጣል፥ ወደ ቃዴስ ምዕ​ራ​ብም ይዞ​ራል።

4 ወደ አጽ​ሞ​ንም ያል​ፋል፤ በግ​ብ​ፅም ሸለቆ በኩል ይወ​ጣል፤ የድ​ን​በ​ሩም መውጫ በባ​ሕሩ አጠ​ገብ ነበረ፤ በደ​ቡብ በኩል ያለው ድን​በ​ራ​ቸው ይህ ነው።

5 በም​ሥ​ራ​ቅም በኩል ያለው ድን​በ​ራ​ቸው እስከ ጨው ባሕር እስከ ዮር​ዳ​ኖ​ስም ነበረ። በሰ​ሜ​ንም በኩል ያለው ድን​በር በዮ​ር​ዳ​ኖስ መጨ​ረሻ እስ​ካ​ለው እስከ ባሕሩ ልሳን ድረስ ነበረ፤

6 ከዚ​ያም ድን​በ​ራ​ቸው ወደ ቤተ ገለ​ዓም ይወ​ጣል፤ በቤ​ት​ዓ​ረባ በሰ​ሜን በኩል ያል​ፋል፤ ድን​በ​ራ​ቸ​ውም ወደ ሮቤል ልጅ ወደ ሊቶን ቢዮን ይወ​ጣል፤

7 ድን​በ​ሩም በአ​ኮር ሸለቆ አራ​ተኛ ክፍል ላይ ይወ​ጣል፤ በአ​ዱ​ሚን ዐቀ​በት ፊት ለፊት፥ በደ​ቡብ በኩል ወዳ​ለ​ችው ወደ ጌል​ገላ ይወ​ር​ዳል፤ ድን​በ​ሩም ወደ ፀሐይ ምንጭ ውኃ ያል​ፋል፤ መው​ጫ​ውም በሮ​ጌል ምንጭ አጠ​ገብ ነበረ፤

8 ድን​በ​ሩም በሄ​ኖም ልጅ ሸለቆ አጠ​ገብ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ወደ​ም​ት​ባ​ለው ወደ ኢያ​ቡስ ወደ ደቡብ ወገን ይወ​ጣል፤ ድን​በ​ሩም በሰ​ሜን በኩል በራ​ፋ​ይም ሸለቆ ዳር ባለው በሄ​ኖም ሸለቆ ፊት ለፊት በባ​ሕር በኩል ወዳ​ለው ተራራ ራስ ላይ ይወ​ጣል፤

9 ድን​በ​ሩም ከተ​ራ​ራው ራስ ወደ ኔፍቶ ውኃ ምንጭ ይሄ​ዳል፤ ወደ ዔፍ​ሮ​ንም ተራራ ይደ​ር​ሳል፤ ወደ ኢያ​ሪም ከተማ ወደ በኣላ ይደ​ር​ሳል።

10 ድን​በ​ሩም ከበ​ኣላ በባ​ሕር በኩል ያል​ፋል፤ ከዚ​ያም በኢ​ያ​ሪም ከተማ ደቡብ በኩ​ልና በኪ​ስ​ሎን ሰሜን በኩል ወደ አሥ​ራ​ቱስ ድን​በር ያል​ፋል፤ በፀ​ሐይ ከተ​ማም ላይ ይወ​ር​ዳል፤ በሊ​ባም በኩል ያል​ፋል።

11 ድን​በ​ሩም ወደ አቃ​ሮን ደቡብ ይወ​ጣል፤ ወደ ሰሜን ወገን ይመ​ለ​ሳል፤ ድን​በሩ ወደ ሰቆት ይወ​ጣል፤ ወደ ደቡ​ብም ያል​ፋል፤ በሌ​ብና በኩ​ልም ይወ​ጣል፤ የድ​ን​በ​ሩም መውጫ በባ​ሕሩ አጠ​ገብ ነበረ።

12 በባ​ሕር በኩል ያለው ድን​በ​ራ​ቸ​ውም እስከ ታላቁ ባሕ​ርና እስከ ዳር​ቻው ድረስ ነበረ። ለይ​ሁዳ ልጆች በየ​ወ​ገ​ና​ቸው በዙ​ሪ​ያው ያለ ድን​በ​ራ​ቸው ይህ ነው።


ካሌብ ኬብ​ሮ​ን​ንና ዳቤ​ርን እንደ ያዘ
( መሳ. 1፥11-15 )

13 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ትእ​ዛዝ ለዮ​ፎኒ ልጅ ለካ​ሌብ በይ​ሁዳ ልጆች መካ​ከል ድር​ሻ​ውን ሰጠው፤ ኢያ​ሱም የዔ​ናቅ ዋና ከተማ የሆ​ነ​ች​ውን የአ​ር​ቦ​ቅን ከተማ ሰጠው። እር​ስ​ዋም ኬብ​ሮን ናት።

14 የዮ​ፎኒ ልጅ ካሌ​ብም ሦስ​ቱን የዔ​ና​ቅን ልጆች ሱሲን፥ ተለ​ሚ​ንና አካ​ሚን ከዚያ አጠ​ፋ​ቸው።

15 ከዚ​ያም ካሌብ በዳ​ቤር ሰዎች ላይ ዘመተ፤ የዳ​ቤ​ርም ስም አስ​ቀ​ድሞ “ሀገረ መጻ​ሕ​ፍት” ነበረ።

16 ካሌ​ብም፥ “ሀገረ መጻ​ሕ​ፍ​ትን ለሚ​መታ፥ ለሚ​ይ​ዛ​ትም ልጄን አክ​ሳን ሚስት ትሆ​ነው ዘንድ እሰ​ጠ​ዋ​ለሁ” አለ።

17 የካ​ሌብ ወን​ድም የቄ​ኔዝ ልጅ ጎቶ​ን​ያል ያዛት፤ ልጁን አክ​ሳ​ንም ሚስት ትሆ​ነው ዘንድ ሰጠው።

18 እር​ስ​ዋም ወደ እርሱ በመ​ጣች ጊዜ “አባ​ቴን እርሻ ልለ​ም​ነው” ብላ አማ​ከ​ረ​ችው፤ እር​ስ​ዋም በአ​ህ​ያዋ ላይ ሆና ጮኸች፤ ካሌ​ብም፥ “ምን ሆንሽ?” አላት።

19 እር​ስ​ዋም፥ “በረ​ከ​ትን ስጠኝ፤ በደ​ቡብ በኩል ያለ​ውን ምድር ሰጥ​ተ​ኸ​ኛ​ልና አሁን ደግሞ የው​ኃ​ውን ምን​ጭ ስ​ጠኝ” አለ​ችው። እር​ሱም የላ​ይ​ኛ​ው​ንና የታ​ች​ኛ​ውን ምንጭ ሰጣት።


የይ​ሁዳ ነገድ ርስት

20 በየ​ወ​ገ​ኖ​ቻ​ቸ​ውም የይ​ሁዳ ልጆች ነገድ ርስት ይህ ነው።

21 በደ​ቡ​ብም በኩል በም​ድ​ራ​ቸው ዳርቻ እስከ ኤዶ​ም​ያስ ድን​በር ያሉት የይ​ሁዳ ልጆች ነገድ ከተ​ሞች እነ​ዚህ ነበሩ፤ ቤሴ​ሌ​ኤል፥ አራ፥ አሦር፤

22 ኤቃም፥ ሬግማ፥ አሩ​ሔል፤

23 ቃዴስ፥ አሶ​ር​ዮ​ስም፤ ሚናን፤

24 በል​ማ​ንና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸ​ውም፤

25 የአ​ሴ​ሮም ከተ​ሞች እር​ስ​ዋም አሶር ናት።

26 ሲን፥ ሰላ​ማዓ፥ ሞላዳ፤

27 ሴሪ፥ ቤፋ​ላድ፤

28 ኮላ​ሴ​ዎል፥ ቤር​ሳ​ቤ​ሕና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው።

29 ባላ፥ ባቆ​ብና አሶም፤

30 ኤለ​ቦ​ሂ​ዳድ፥ ቤቴ​ልና ኤር​ማም፤

31 ሴቄ​ላቅ፥ ማኬ​ሪ​ምር፥ ሴቱ​ናቅ፤

32 ላቦስ ሳሌ፥ ኤር​ሞ​ትም ሃያ ዘጠኝ ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው።

33 በቆ​ላው፥ አስ​ጣል፥ ሳራዓ፥ አሳ፤

34 ራሜ፥ ጣኖ፥ ኢዱ​ቶት፥ መሐ​ንስ፤

35 ኤር​ሙት፥ ኤዶ​ላም፥ ሜም​ብራ፥ ሰአክ፥ አዚቃ፤

36 ሴቃ​ርም፥ ጋዴ​ርና ሰፈ​ሮ​ችዋ፥ ዐሥራ አራት ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው።

37 ሴና፥ አዳ​ሶን፥ ማጋ​ዳ​ል​ጋድ፤

38 አዶ​ላል፥ መሴፋ፥ ይቃ​ሩል፥ ለኪስ፤

39 በሴ​ዶት ይዴሃ፥ ደል​ያም፤

40 ኮብራ፥ ማኬስ፥ መሐ​ኮ​ስም፤

41 ጌዶር፥ በጋ​ድ​ያል፥ ኖማን፥ መቄ​ዶም፥ ዐሥራ ስድ​ስት ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው።

42 ሌምና፥ ኤተቅ፥ አኖክ፥

43 ኢድና ናሲ​ብም፤

44 ኤላም፥ አቁ​ዛም፥ ኬዜብ ቴርሳ፥ ኤሎ​ምም፥ ዐሥር ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው።

45 አቃ​ሮን ከመ​ን​ደ​ሮ​ች​ዋና ከመ​ሰ​ማ​ሪ​ያ​ዎ​ችዋ ጋር።

46 ከአ​ቃ​ሮ​ንና ከጌ​ምና ጀምሮ በአ​ሴ​ዶት አቅ​ራ​ቢያ ያሉ ሁሉና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው፤

47 አሴ​ያ​ዶት መን​ደ​ሮ​ች​ዋና መሰ​ማ​ሪ​ያ​ዎ​ች​ዋም፥ ጋዛም መን​ደ​ሮ​ች​ዋና መሰ​ማ​ሪ​ያ​ዎ​ች​ዋም እስከ ግብፅ ወንዝ ድረስ፥ ታላቁ ባሕ​ርም ወሰኑ ነው።

48 የሳ​ምር ተራ​ራ​ዎች ፥ ኢዩ​ቴር፥ ሦካ፤

49 ሬና፥ የመ​ጽ​ሐፍ ሀገር የሆ​ነች ዳቤር፤

50 አኖን፥ ሴቄማ፥ ኤሳ​ማም፤

51 ጎሶም ከሉም፥ ከናም፥ ዐሥራ አንድ ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው።

52 ኤሬም፥ ሬምና፥ ሶማ፤

53 ኢያ​ማ​ይን፥ ቤታ​ቁም፥ ፋቁሕ፤

54 ኤውማ፥ የአ​ር​ቦቅ ከተማ እር​ስ​ዋም ኬብ​ሮን ናት፥ ሶሬት፥ ዘጠኝ ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው።

55 ማሖር፥ ኬር​ሜል፥ አዚብ፥ ኢጣን፤

56 ኢያ​ሬ​ዬል፥ ኢያ​ሪ​ቅም፥ ዘቃ​ይ​ንም፤

57 ጋባ፥ ተምና፥ ዘጠኝ ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው።

58 አሌዋ፥ ቤተ​ሱር፥ ጌዶር፤

59 ማዕ​ራት፥ ቤት​አ​ኖት፥ ኤል​ት​ቆን፥ ስድ​ስት ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው።

60 ቴቆ፥ ኤፍ​ራታ፥ ይኽ​ች​ውም ቤተ ልሔም ናት፤ ፋጎ​ርም፥ ኤጣ​ንም፥ ቁሎን፥ ጠጦ​ንም፥ ሶብ​ሄም፥ ቃሬም፥ ጌሌም፥ ኤቴር፥ መነ​ኮም፥ ዐሥራ አንድ ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው፥ ቅር​ያ​ት​በ​ኣል፥ ይኽ​ች​ውም የኢ​ያ​ርም ከተማ ናት፤ ሶቤታ፥ ሁለቱ ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው።

61 ባዳ​ር​ጊስ፥ ተራ​ብ​ዐ​ምም፥ ኤኖን፤ ሴኬ​ዎ​ዛን፥

62 ናፍ​ላ​ዛ​ንና ከተ​ሞ​ቻ​ቸው፥ ሳዶን፥ አቃ​ዴስ፥ ሰባት ከተ​ሞ​ችና መን​ደ​ሮ​ቻ​ቸው።

63 በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም የተ​ቀ​መ​ጡ​ትን ኢያ​ቡ​ሴ​ዎ​ና​ው​ያ​ንን ግን የይ​ሁዳ ልጆች ሊያ​ሳ​ድ​ዱ​አ​ቸው አል​ተ​ቻ​ላ​ቸ​ውም፤ ኢያ​ቡ​ሴ​ዎ​ና​ው​ያ​ንም እስከ ዛሬ ድረስ በይ​ሁዳ ልጆች መካ​ከል በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ውስጥ ተቀ​ም​ጠ​ዋል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች