Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

ትን​ቢተ ዳን​ኤል 11 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 “እኔም በሜ​ዶ​ና​ዊው በዳ​ር​ዮስ መጀ​መ​ሪያ ዓመት አጸ​ና​ውና አበ​ረ​ታው ዘንድ ቆሜ ነበር።

2 “አሁ​ንም እው​ነ​ትን እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ። እነሆ ሦስት ነገ​ሥ​ታት ደግሞ በፋ​ርስ ይነ​ሣሉ፤ አራ​ተ​ኛ​ውም ከሁሉ ይልቅ እጅግ ባለ​ጸጋ ይሆ​ናል፤ በባ​ለ​ጸ​ግ​ነ​ቱም በበ​ረታ ጊዜ በግ​ሪክ መን​ግ​ሥት ላይ ሁሉን ያስ​ነ​ሣል።

3 ኀያ​ልም ንጉሥ ይነ​ሣል፤ ትልቅ አገ​ዛ​ዝ​ንም ይገ​ዛል፤ እንደ ፈቃ​ዱም ያደ​ር​ጋል።

4 በተ​ነ​ሣም ጊዜ መን​ግ​ሥቱ ትሰ​በ​ራ​ለች፤ በአ​ራ​ቱም ነፋ​ሳት ትበ​ተ​ና​ለች፤ ለዘሩ ግን አይ​ከ​ፋ​ፈ​ልም፤ ከእ​ር​ሱም በኋላ እርሱ እንደ ገዛ​በት አገ​ዛዝ አይ​ሆ​ንም፤ መን​ግ​ሥቱ ታል​ፋ​ለች፤ ከእ​ነ​ዚ​ህም ለሌ​ሎች ትሰ​ጣ​ለች።

5 “የአ​ዜ​ብም ንጉሥ ይበ​ረ​ታል፤ ከአ​ለ​ቆ​ቹም አንዱ በእ​ርሱ ላይ ይበ​ረ​ታል፤ ከእ​ር​ሱም ይልቅ ብዙ ግዛ​ትን ይገ​ዛል።

6 ከዘ​መ​ና​ትም በኋላ ይቀ​ላ​ቀ​ላሉ፤ የአ​ዜ​ብም ንጉሥ ሴት ልጅ ቃል ኪዳን ለማ​ድ​ረግ ወደ መስዕ ንጉሥ ትመ​ጣ​ለች። የክ​ን​ድዋ ኀይል ግን አይ​ጸ​ናም፤ ዘሩም አይ​ጸ​ናም፤ እር​ስ​ዋና እር​ስ​ዋን ያመጡ፥ የወ​ለ​ዳ​ትም፥ በዚ​ያም ዘመን ያጸ​ናት አል​ፈው ይሰ​ጣሉ።

7 ነገር ግን ከሥ​ርዋ ቍጥ​ቋጥ አንዱ በስ​ፍ​ራው ይነ​ሣል፤ ወደ ሠራ​ዊ​ቱም ይመ​ጣል፤ ወደ መስ​ዕም ንጉሥ አምባ ይገ​ባል፤ በላ​ያ​ቸ​ውም ያደ​ር​ጋል፤ ያሸ​ን​ፍ​ማል።

8 አማ​ል​ክ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንና ቀል​ጠው የተ​ሠ​ሩ​ትን ምስ​ሎ​ቻ​ቸ​ውን ከብ​ርና ከወ​ር​ቅም የተ​ሠ​ሩ​ትን የከ​በ​ሩ​ትን ዕቃ​ዎች ወደ ግብፅ ይማ​ር​ካል፤ እር​ሱም ከመ​ስዕ ንጉሥ በላይ ሆኖ ይቆ​ማል።

9 ይህም ወደ አዜብ ንጉሥ መን​ግ​ሥት ይገ​ባል፥ ነገር ግን ወደ ገዛ ምድሩ ይመ​ለ​ሳል።

10 “ልጆ​ቹም ይዋ​ጋሉ፤ ብዙ ሕዝ​ብ​ንና ሠራ​ዊ​ትን ይሰ​በ​ስ​ባሉ፤ እር​ሱም ይመ​ጣል፤ ይበ​ረ​ታ​ማል፤ ያል​ፍ​ማል፤ ተመ​ል​ሶም እስከ አም​ባው ድረስ ይዋ​ጋል።

11 የአ​ዜ​ብም ንጉሥ ይቈ​ጣል፤ ወጥ​ቶም ከመ​ስዕ ንጉሥ ጋር ይዋ​ጋል፤ ብዙ ሕዝ​ብ​ንም ለሰ​ልፍ ያቆ​ማል፤ ሕዝ​ቡም አልፎ በእጁ ይሰ​ጣል።

12 ሕዝ​ቡ​ንም ይወ​ስ​ዳል፤ ልቡ​ንም ያስ​ታ​ብ​ያል፤ አእ​ላ​ፋ​ት​ንም ይጥ​ላል፤ ነገር ግን አያ​ሸ​ን​ፍም።

13 የመ​ስ​ዕም ንጉሥ ይመ​ለ​ሳል፥ ከቀ​ደ​መ​ውም የበ​ለጠ ብዙ ሕዝ​ብን ያቆ​ማል፤ በዘ​መ​ና​ትና በዓ​መ​ታ​ትም ፍጻሜ ከታ​ላቅ ሠራ​ዊ​ትና ከብዙ ሀብት ጋር ይመ​ጣል።

14 በዚ​ያም ዘመን ብዙ ሰዎች በአ​ዜብ ንጉሥ ላይ ይነ​ሣሉ፤ ከሕ​ዝ​ብ​ህም መካ​ከል የዐ​መፅ ልጆች ራእ​ዩን ያጸኑ ዘንድ ይነ​ሣሉ፤ ነገር ግን ይወ​ድ​ቃሉ።

15 የመ​ስ​ዕም ንጉሥ ይመ​ጣል፤ አፈ​ር​ንም ይደ​ለ​ድ​ላል፤ የተ​መ​ሸ​ገ​ች​ንም ከተማ ይይ​ዛል፤ የአ​ዜ​ብም ክንድ የተ​መ​ረ​ጡ​ትም ሕዝብ አይ​ቆ​ሙም፤ ለመ​ቋ​ቋ​ምም ኀይል የላ​ቸ​ውም።

16 ወደ እርሱ የሚ​መ​ጣው እንደ ፈቃዱ ያደ​ር​ጋል፤ በፊ​ቱም የሚ​ቆም የለም፤ በመ​ል​ካ​ሚ​ቱም ምድር ይቆ​ማል፤ ሁሉም በእጁ ይፈ​ጸ​ማል።

17 ከመ​ን​ግ​ሥ​ቱም ሁሉ ኀይል ጋር ይመጣ ዘንድ ፊቱን ያቀ​ናል፤ ከእ​ር​ሱም ጋር አን​ድ​ነ​ትን ያደ​ር​ጋል፤ ለጥ​ፋ​ቱም ሴት ልጅ ትሰ​ጠ​ዋ​ለች፤ እር​ስ​ዋም አት​ጸ​ናም፤ ለእ​ር​ሱም አት​ሆ​ንም።

18 ከዚ​ህም በኋላ ፊቱን ወደ ደሴ​ቶች ይመ​ል​ሳል፤ ብዙ​ዎ​ች​ንም ይወ​ስ​ዳል፤ የኀ​ፍ​ረት አለ​ቆ​ቹ​ንም ይሽ​ራል፤ ኀፍ​ረ​ቱም በላዩ ይመ​ለ​ሳል።

19 ፊቱ​ንም ወደ ገዛ ምድሩ አን​ባ​ዎች ይመ​ል​ሳል፤ ደክ​ሞም ይወ​ድ​ቃል፤ አይ​ገ​ኝ​ምም።

20 “የመ​ን​ግ​ሥ​ትን ሥል​ጣ​ንና ክብር የሚ​ሽር ይነ​ሣል፤ በመ​ን​በ​ሩም ይቀ​መ​ጣል፤ ነገር ግን በቍ​ጣም ሳይ​ሆን፥ በጦ​ር​ነ​ትም ሳይ​ሆን ከጥ​ቂት ቀን በኋላ ይሰ​በ​ራል።


ጨካኙ የሶ​ርያ ንጉሥ

21 በእ​ር​ሱም ስፍራ የተ​ጠቃ ሰው ይነ​ሣል፤ የመ​ን​ግ​ሥ​ቱ​ንም ክብር አይ​ሰ​ጡ​ትም፤ በቀ​ስታ ይመ​ጣል፤ መን​ግ​ሥ​ት​ንም በማ​ታ​ለል ይይ​ዛል።

22 የሚ​ጐ​ርፉ ተዋ​ጊ​ዎ​ቹም ክን​ዶች ከፊቱ ይሰ​በ​ራሉ፤ እር​ሱና የቃል ኪዳኑ አለ​ቃም ይሰ​በ​ራሉ።

23 ከእ​ር​ሱም ጋር ከተ​ወ​ዳጀ በኋላ ተን​ኰ​ልን ያደ​ር​ጋል፤ ከጥ​ቂ​ትም ሕዝብ ጋር ወጥቶ ይበ​ረ​ታል።

24 በቀ​ስ​ታም ከሀ​ገር ሁሉ ወደ ለመ​ለ​መ​ችው ክፍል ይገ​ባል፤ አባ​ቶ​ቹና የአ​ባ​ቶቹ አባ​ቶች ያላ​ደ​ረ​ጉ​ት​ንም ያደ​ር​ጋል፤ ብዝ​በ​ዛ​ው​ንና ምር​ኮ​ውን፥ ሀብ​ቱ​ንም በመ​ካ​ከ​ላ​ቸው ይበ​ት​ናል፤ በም​ሽ​ጎ​ችም ላይ እስከ ጊዜው ድረስ ዐሳ​ቡን ይፈ​ጥ​ራል።

25 በታ​ላ​ቅም ሠራ​ዊት ሆኖ ኀይ​ሉ​ንና ልቡን በአ​ዜብ ንጉሥ ላይ ያስ​ነ​ሣል፤ የአ​ዜ​ብም ንጉሥ በታ​ላ​ቅና በብዙ ሠራ​ዊት ይበ​ረ​ታል፤ ነገር ግን ዐሳብ በእ​ርሱ ላይ ይፈ​ጥ​ራ​ሉና አይ​ጸ​ናም።

26 መብ​ሉ​ንም የሚ​በሉ ሰዎች ይሰ​ብ​ሩ​ታል፤ ሠራ​ዊ​ቱም ይጐ​ር​ፋል፤ ብዙ​ዎ​ችም ተገ​ድ​ለው ይወ​ድ​ቃሉ።

27 እነ​ዚ​ህም ሁለት ነገ​ሥ​ታት በል​ባ​ቸው ክፋ​ትን ያደ​ር​ጋሉ፤ በአ​ንድ ገበ​ታም ተቀ​ም​ጠው ሐሰ​ትን ይና​ገ​ራሉ፤ ገና ጊዜው አል​ደ​ረ​ሰ​ምና አይ​ከ​ና​ወ​ን​ላ​ቸ​ውም።

28 “ከብ​ዙም ሀብት ጋር ወደ ምድሩ ይመ​ለ​ሳል፥ ልቡም በተ​ቀ​ደ​ሰው ቃል ኪዳን ላይ ይሆ​ናል፤ ፈቃ​ዱ​ንም ያደ​ር​ጋል፥ ወደ ገዛ ምድ​ሩም ይመ​ለ​ሳል።

29 በተ​ወ​ሰ​ነ​ውም ጊዜ ይመ​ለ​ሳል፤ ወደ አዜ​ብም ይመ​ጣል፤ ነገር ግን የኋ​ለ​ኛው እንደ ፊተ​ኛው አይ​ሆ​ንም።

30 ጺም፥ ከይ​ተ​ምና ኔባእ በእ​ርሱ ላይ ይመ​ጣሉ ስለ​ዚህ አዝኖ ይመ​ለ​ሳል፥ በቅ​ዱ​ሱም ቃል ኪዳን ላይ ይቈ​ጣል፤ ፈቃ​ዱ​ንም ያደ​ር​ጋል፤ ተመ​ል​ሶም ቅዱ​ሱን ቃል ኪዳን የተ​ዉ​ትን ሰዎች ይመ​ለ​ከ​ታል።

31 ዘሮ​ችም ከእ​ርሱ ይነ​ሣሉ፤ ቤተ መቅ​ደ​ሱ​ንም ያረ​ክ​ሳሉ፤ የዘ​ወ​ት​ሩ​ንም መሥ​ዋ​ዕት ያስ​ቀ​ራሉ፤ የጥ​ፋ​ት​ንም ርኵ​ሰት ያቆ​ማሉ።

32 ቃል ኪዳ​ኑን የሚ​በ​ድ​ሉ​ት​ንም በማ​ታ​ለል ያስ​ታሉ፤ ነገር ግን አም​ላ​ካ​ቸ​ውን የሚ​ያ​ውቁ ሕዝብ ይበ​ረ​ታሉ፤ ያደ​ር​ጋ​ሉም።

33 በሕ​ዝ​ቡም መካ​ከል ያሉ ጥበ​በ​ኞች ብዙ ሰዎ​ችን ያስ​ተ​ም​ራሉ፤ ነገር ግን በሰ​ይ​ፍና በእ​ሳት ነበ​ል​ባል በም​ር​ኮና በብዙ ዘመን ብዝ​በዛ ይደ​ክ​ማሉ።

34 በመ​ከ​ራም ጊዜ በጥ​ቂት ርዳታ ይረ​ዳሉ፤ ብዙ ሰዎ​ችም በግ​ብ​ዝ​ነት ወደ እነ​ርሱ ይጨ​መ​ራሉ።

35 ጊዜው ገና አል​ደ​ረ​ሰ​ምና ያግ​ሏ​ቸው፥ ያነ​ጿ​ቸ​ውና ያጠ​ሯ​ቸው ዘንድ ከዐ​ዋ​ቂ​ዎች እኩ​ሌ​ቶቹ እስከ ጊዜው ድረስ መከራ ይቀ​በ​ላሉ፤ በከ​በረ ቦታ የሚ​ቆም፥ መጽ​ሐ​ፍ​ንም የሚ​ያ​ነ​ብብ ሰው ይህን ነገር ልብ ያድ​ርግ።

36 “ንጉ​ሡም እንደ ፈቃዱ ያደ​ር​ጋል፤ ራሱ​ንም ከፍ ከፍ ያደ​ር​ጋል፤ በአ​ማ​ል​ክት ሁሉ ላይ ራሱን ታላቅ ያደ​ር​ጋል፤ በአ​ማ​ል​ክ​ትም አም​ላክ ላይ በት​ዕ​ቢት ይና​ገ​ራል፤ ቍጣም እስ​ኪ​ፈ​ጸም ድረስ ይከ​ና​ወ​ን​ለ​ታል፤ የተ​ወ​ሰ​ነው ይደ​ረ​ጋ​ልና።

37 የአ​ባ​ቶ​ቹ​ንም አም​ላክ፥ የሴ​ቶ​ች​ንም ምኞት አያ​ከ​ብ​ርም፤ ራሱ​ንም በሁሉ ላይ ታላቅ ያደ​ር​ጋ​ልና አማ​ል​ክ​ትን ሁሉ አያ​ው​ቅም።

38 ጽኑዕ በሆነ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሥል​ጣ​ንም ይኰ​ራል፤ አባ​ቶ​ቹም ያላ​ወ​ቁ​ትን አም​ላክ በወ​ር​ቅና በብር፥ በዕ​ን​ቍና በከ​በረ ነገር ያከ​ብ​ረ​ዋል።

39 ከባ​ዕ​ድም አም​ላክ ጋር የተ​መ​ሸጉ ጽኑ አም​ባ​ዎ​ችን ያደ​ር​ጋል፤ ክብ​ርን ያበ​ዛ​ላ​ቸ​ዋል፤ በብ​ዙም ላይ ያስ​ገ​ዛ​ቸ​ዋል፤ ምድ​ር​ንም በዋጋ ይከ​ፍ​ላል።

40 “በፍ​ጻሜ ዘመ​ንም የዐ​ዜብ ንጉሥ ከእ​ርሱ ጋር ይዋ​ጋል፤ የመ​ስ​ዕም ንጉሥ ከሠ​ረ​ገ​ሎ​ችና ከፈ​ረ​ሰ​ኞች፥ ከብዙ መር​ከ​ቦ​ችም ጋር ይመ​ጣ​በ​ታል፤ ወደ ሀገ​ሮ​ችም ይገ​ባል፤ ይጐ​ር​ፍ​ማል፥ ያል​ፍ​ማል።

41 ወደ መል​ካ​ሚ​ቱም ምድር ይገ​ባል፤ ብዙ ሀገ​ሮ​ችም ይወ​ድ​ቃሉ፤ ነገር ግን ኤዶ​ም​ያ​ስና ሞዓብ፥ ከአ​ሞ​ንም ልጆች የበ​ለ​ጡት ከእጁ ይድ​ናሉ።

42 እጁን በሀ​ገ​ሮች ላይ ይዘ​ረ​ጋል፤ የግ​ብ​ፅም ምድር ከእጁ አታ​መ​ል​ጥም።

43 በወ​ር​ቅና በብ​ርም መዝ​ገብ ላይ ፥ በከ​በ​ረ​ችም በግ​ብፅ ዕቃ ሁሉ ላይ ይሠ​ለ​ጥ​ናል፤ የሊ​ብ​ያና የኢ​ት​ዮ​ጵያ ሰዎ​ችም ረዳ​ቶች ይሆ​ኑ​ታል።

44 ከም​ሥ​ራ​ቅና ከሰ​ሜን ግን ወሬ ይደ​ር​ሰ​ዋል፤ ይቸ​ኩ​ላ​ልም፤ ብዙ ሰዎ​ች​ንም ይገ​ድ​ልና ፈጽሞ ያጠፋ ዘንድ በታ​ላቅ ቍጣ ይወ​ጣል።

45 ንጉ​ሣዊ ድን​ኳ​ኑ​ንም በባ​ሕ​ርና በከ​በ​ረው በቅ​ዱሱ ተራራ መካ​ከል ይተ​ክ​ላል፤ እስከ ጊዜ​ውም ይበ​ረ​ታል። የሚ​ረ​ዳ​ውም የለም።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች