Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ሣልስ 4 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ጌታ​ውም አዳ​ምን ይቤ​ዠው ዘንድ አለው፤ አን​ተ​ንም ያሳ​ፍ​ር​ሃል፤ በጉ​ንም ከተ​ኵላ አፍ ያድ​ነ​ዋል።

2 ነገር ግን አንተ የገ​ዛ​ሃ​ቸ​ውን ሰዎች ከአ​ንተ ጋር ይዘህ ወደ ጥፋት ትሄ​ዳ​ለህ።

3 የፈ​ጣ​ሪ​ያ​ቸው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሕግ የጠ​በቁ ግን የእ​ርሱ እድል ፋንታ ያደ​ር​ጋ​ቸው ዘንድ፥ የፈ​ጣ​ሪ​ያ​ቸው የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ሕግ እን​ዳ​ንተ ካል​ተ​ላ​ለፉ ከቅ​ዱ​ሳን መላ​እ​ክቱ ጋር ያመ​ሰ​ግ​ኑት ዘንድ ከክፉ ሥራህ ከሰ​ወ​ራ​ቸው ከፈ​ጣ​ሪ​ያ​ቸው ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጋር ደስ ይላ​ቸ​ዋል።

4 አንተ ግን ከመ​ላ​እ​ክቱ ጋራ ታመ​ሰ​ግ​ነው ዘንድ እንደ አንተ ካሉት ሁሉ ይልቅ መርጦ የሰ​ጠህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በት​ዕ​ቢ​ትህ ከፍ ያለ ዙፋ​ንን ነሳህ።

5 አን​ተም ታበ​ይህ፤ ዲያ​ብ​ሎ​ስም ተባ​ልህ፤ ሠራ​ዊ​ቶ​ች​ህም አጋ​ን​ንት ተባሉ።

6 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ወዱ ግን እንደ ቅዱ​ሳን መላ​እ​ክት ለእ​ርሱ ወገ​ኖቹ ይሆ​ናሉ፤ የሚ​ያ​መ​ሰ​ግ​ኑት ሱራ​ፌ​ልና ኪሩ​ቤ​ልም ክን​ፎ​ቻ​ቸ​ውን ዘር​ግ​ተው ያለ​ማ​ቋ​ረጥ ያመ​ሰ​ግ​ናሉ።

7 አንተ ግን በመ​ል​ክህ ከተ​ፈ​ጠሩ ከነ​ገ​ድ​ህና ከሠ​ራ​ዊ​ትህ ጋር ሁል​ጊዜ ታመ​ሰ​ግ​ነው ዘንድ ምስ​ጋ​ና​ህን በት​ዕ​ቢ​ት​ህና በስ​ን​ፍ​ናህ አጠ​ፋህ።

8 እንደ አንተ ያለ መፍ​ጠር የማ​ይ​ቻ​ለው መስ​ሎህ አንተ የፈ​ጠ​ረህ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ምስ​ጋና በዘ​ነ​ጋህ ጊዜ፥ ዐሥ​ረኛ ነገድ አድ​ርጎ የፈ​ጠ​ረህ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምስ​ጋ​ናው እን​ዳ​ይ​ጐ​ድል አን​ተም ከወ​ን​ድ​ሞ​ችህ አን​ድ​ነት በተ​ለ​የህ ጊዜ የፈ​ጠ​ረህ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምስ​ጋ​ናው እን​ዳ​ይ​ጐ​ድል፥

9 አን​ተም በል​ቡ​ናህ ትዕ​ቢት የፈ​ጠ​ረህ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ምስ​ጋና ቸል ባልህ ጊዜ፥ እር​ሱም በተ​ቈ​ጣ​ህና፤ በተ​ዘ​ባ​በ​ተ​ብህ ጊዜ፤ ከሠ​ራ​ዊ​ቶ​ች​ህም ጋራ በገ​ሃ​ነም እን​ቅ​ጥ​ቅጥ በአ​ጋ​ዘህ ጊዜ

10 በቅ​ዱ​ሳት እጆቹ ከም​ድር መሬ​ትን ወሰደ፤ ውኃ​ንና እሳ​ትን፥ ነፋ​ስ​ንም ጨመረ፤ አዳ​ም​ንም በመ​ል​ኩና በም​ሳ​ሌው ፈጠ​ረው።

11 ምስ​ጋ​ናው በአ​ንተ ጉድ​ለት ይመላ ዘንድ በእጁ በፈ​ጠ​ረው ፍጥ​ረት ሁሉ ላይ ሾመው። የመ​ሬ​ታ​ዊ​ውም ምስ​ጋና ከሰ​ማ​ያ​ው​ያኑ ምስ​ጋና ጋር ተጨ​መረ፤ ምስ​ጋ​ና​ቸ​ውም እኩል ሆነ።

12 አንተ ግን በት​ዕ​ቢ​ት​ህና በአ​ን​ገ​ትህ መደ​ን​ደን ተሰ​ደ​ድህ፤ ከፈ​ጠ​ረህ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ጌት​ነት ወጥ​ተህ ራስ​ህን አጠ​ፋህ።

13 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ነቱ ምስ​ጋና እን​ዳ​ይ​ጐ​ድል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በፈ​ቃዱ ምክር የሚ​ያ​መ​ሰ​ግ​ነ​ውን ፈጥ​ሯ​ልና ምስ​ጋ​ናው እን​ዳ​ይ​ጐ​ድል ዕወቅ።

14 እርሱ ሳይ​ደ​ረግ ሁሉን ያው​ቃ​ልና፥ ትእ​ዛ​ዙ​ንም እን​ደ​ም​ታ​ፈ​ርስ ሳይ​ፈ​ጥ​ርህ ዐወ​ቀህ፤ ዓለም ሳይ​ፈ​ጠር በእ​ርሱ ዘንድ የተ​ሰ​ወረ ምክር ነበ​ረና በካ​ድ​ኸው ጊዜ ባር​ያው አዳ​ምን በመ​ል​ኩና በም​ሳ​ሌው ፈጠ​ረው።

15 ሰሎ​ሞን፥ “ከኮ​ረ​ብ​ቶች በፊት ወለ​ደኝ፤ ዓለ​ምም ሳይ​ከ​ና​ወን የም​ድ​ርም መሠ​ረት ሳይ​መ​ሠ​ረት፥

16 የተ​ራ​ራ​ዎ​ችና የኮ​ረ​ብ​ቶች መቋ​ምያ ሳይ​ተ​ከል፥ የዓ​ለ​ምም ጐዳና ሳይ​ጸና፥ የፀ​ሐ​ይና የጨ​ረቃ ብር​ሃን ሳይ​በራ፥ የከ​ዋ​ክ​ብ​ትና የዘ​መ​ኖች ምግ​ብና ሳይ​ታ​ወቅ፥

17 ሌሊ​ትና መዓ​ልት ሳይ​ፈ​ራ​ረቁ፥ ባሕ​ርም ባሸዋ ሳት​ወ​ሰን፥ የተ​ፈ​ጠ​ረው ፍጥ​ረት ሁሉ ሳይ​ፈ​ጠር፥

18 ዛሬም የሚ​ታ​የው ሁሉ ሳይ​ታይ፥ ዛሬ የሚ​ጠ​ራው ስም ሁሉ ሳይ​ጠራ ፈጠ​ረኝ” ብሎ እንደ ተና​ገረ፥ አን​ተና እን​ዳ​ንተ ያሉ መላ​እ​ክት፥ ባር​ያው አዳ​ምም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኅሊና ውስጥ ነበ​ራ​ችሁ።

19 አንተ በካ​ድህ ጊዜ ቅዱስ ስሙ ይመ​ሰ​ገን ዘንድ፥ አን​ተም በታ​በ​ይህ ጊዜ ከመ​ሬት በፈ​ጠ​ረው በተ​ዋ​ረደ በባ​ር​ያው በአ​ዳም ይመ​ሰ​ገን ዘንድ አዳ​ምን ፈጠ​ረው።

20 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የድ​ሆ​ችን ጸሎት ከሩቅ ይሰ​ማ​ልና፥ የተ​ዋ​ረዱ ሰዎ​ች​ንም ምስ​ጋና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይወ​ዳ​ልና።

21 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የት​ዕ​ቢ​ተ​ኞ​ችን ነገር ቸል ይላል፥ የፈ​ረ​ስን ኀይል አይ​ወ​ድ​ምና፥ በሰው ጕል​በ​ትም ደስ አይ​ለ​ው​ምና።

22 ነገር ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሚ​ፈ​ሩ​ትና ስለ ኀጢ​አ​ታ​ቸው ጩኸው በሚ​ያ​ለ​ቅሱ ደስ ይለ​ዋል።

23 አንተ በን​ስሓ መና​ዘዝ ተሳ​ነህ።

24 ያ መሬት ግን ስለ ኀጢ​አቱ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ፈጽሞ እያ​ለ​ቀሰ በን​ስሓ ተመ​ለሰ።

25 አን​ተስ በል​ብህ ትዕ​ቢ​ትና በአ​ን​ገ​ትህ መደ​ን​ደን የሰ​ላም መን​ገ​ድን አላ​ወ​ቅ​ሃ​ትም፥ ንስ​ሓ​ንም አላ​ወ​ቅ​ሃ​ትም፥ በን​ስሓ፥ በል​ቅ​ሶና በእ​ንባ በፈ​ጣ​ሪህ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት መና​ዘዝ ተሳ​ነህ።

26 ያ አመ​ድና መሬት የሆነ ድሃ ግን በል​ቅ​ሶና በእ​ንባ ወደ ንስሓ፥ ወደ ሰላ​ምና ወደ ትሕ​ትና መን​ገድ ተመ​ለሰ።

27 አን​ተስ ለፈ​ጠ​ረህ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ራስ​ህ​ንና የል​ብ​ህን ቀፈት አላ​ዋ​ረ​ድ​ህም።

28 እርሱ ግን በበ​ደ​ለው በደል ራሱን አዋ​ርዶ ተና​ዘዘ፤ አል​ታ​በ​የ​ምም።

29 ያንም ስሕ​ተት የፈ​ጠ​ረው እርሱ አይ​ደ​ለም። ከአ​ንተ የተ​ገኘ ነው እንጂ፥ ወን​ጀ​ልን ፈጥ​ረህ አው​ጥ​ተ​ኸ​ዋ​ልና። በት​ዕ​ቢ​ት​ህም ከአ​ንተ ጋራ ወደ አንተ ጥፋት ወሰ​ድ​ኸው።

30 ሁለ​ታ​ች​ሁን ሁሉ ሳይ​ፈ​ጥ​ራ​ችሁ ዐው​ቋ​ች​ኋ​ልና፥ አካ​ሄ​ዳ​ች​ሁ​ንም ዐው​ቋ​ልና ይህ የተ​ደ​ረገ በል​ብህ ትዕ​ቢት እንደ ሆነ እርሱ ያው​ቃል።

31 ያን የት​ዕ​ቢት ተን​ኰል የሌ​ለ​ውን ግን በን​ስሓ፥ በል​ቅ​ሶና በእ​ንባ መለ​ሰው።

32 አንተ ግን በል​ብህ ትዕ​ቢት በን​ስሓ መና​ዘዝ ተሳ​ነህ። በድሎ በን​ስሓ የማ​ይ​ና​ዘዝ ሰው ከቀ​ድሞ በደሉ ይልቅ በደ​ሉን ያከ​ፋ​ልና።

33 ነገር ግን በድሎ በፈ​ጣ​ሪው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት የሚ​ና​ዘ​ዝና የሚ​ያ​ለ​ቅስ፥ እርሱ በእ​ው​ነት ንስሓ ገባ፤ የጌ​ታ​ው​ንም ልብ ያራራ ዘንድ የመ​ዳ​ኑን መን​ገድ አገኘ፤ በጌ​ታ​ውም ፊት ተና​ዘዘ፤ ጌታ​ውም በባ​ሪ​ያው ላይ ይቈጣ ዘንድ ቀድሞ ከመ​ከ​ረ​በት ያቃ​ል​ል​ለ​ታል፤ በብዙ ንስ​ሓና ስግ​ደት ተና​ዝ​ዞ​አ​ልና። የቀ​ደመ ኀጢ​አ​ቱ​ንም ይቅር ይለ​ዋል።

34 ወደ ቀደመ በደ​ሉም ካል​ተ​መ​ለሰ፥ ይህ​ንም ካደ​ረገ ይህ ፍጹም ንስሓ ነው። አዳ​ምስ ፈጣ​ሪ​ውን ማሰ​ብ​ንና ለፈ​ጣ​ሪው መና​ዘ​ዝን አል​ዘ​ነ​ጋም።

35 አን​ተም ለፈ​ጣ​ሪህ በን​ስሓ ተና​ዘዝ፤ በእ​ርሱ ላይና በእጁ ሥራ ላይም በደ​ልን አታ​ብዛ፤ እነ​ርሱ ሥጋ​ው​ያ​ንና ደማ​ው​ያን ስለ ሆኑ የፈ​ጠ​ራ​ቸው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ድካ​ማ​ቸ​ውን ያው​ቃ​ልና።

36 ነፍ​ሳ​ቸ​ውም ከተ​ለ​የች በኋላ ሥጋ​ቸው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እስ​ከ​ፈ​ቀ​ዳት ቀን ድረስ ትቢያ ይሆ​ናል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች