Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ሣልስ 3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ለአ​ን​ተስ ፈጣ​ሪህ ወደ​ላ​ከህ እየ​ተ​ላ​ክህ ፈጽ​መህ ታመ​ሰ​ግን ዘንድ አንድ አሳ​ብን ፈጠ​ረ​ልህ።

2 ለአ​ዳም ግን ክፉ የሆኑ አም​ስት አሳ​ቦ​ችና በጎ የሆኑ አም​ስት አሳ​ቦች ዐሥር አሳ​ቦች ተሰ​ጡት።

3 ዳግ​መ​ኛም እንደ ባሕር ሞገድ፥ ከም​ድ​ርም አን​ሥቶ ትቢ​ያን እን​ደ​ሚ​በ​ትን ጥቅል ነፋስ፥ ነፋ​ስም እን​ደ​ሚ​ያ​ና​ው​ጠው እንደ ባሕር ሞገድ የሚ​ታ​ወኩ ብዙ አሳ​ቦች አሉት፤ እን​ደ​ማ​ይ​ቈ​ጠር እንደ ዝና​ብም ጠብታ በልቡ ከአለ ከማ​ይ​ቈ​ጠር ከአ​ሳቡ ብዛት የተ​ነሣ የአ​ዳም አሳብ እን​ደ​ዚሁ ነው።

4 የአ​ንተ ግን አሳ​ብህ አን​ዲት ናት፤ ሥጋዊ አይ​ደ​ለ​ህ​ምና ሌላ አሳብ የለ​ህም።

5 አንተ ግን በእ​ባብ ልቡና አድ​ረህ አንድ አካል የሆነ አዳ​ምን በክፉ ሽን​ገላ አጠ​ፋ​ኸው፤ ሔዋ​ንም የእ​ባ​ብን ነገር ሰማች፤ ሰም​ታም እን​ዳ​ዘ​ዘ​ቻት አደ​ረ​ገች።

6 መጥ​ታም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መጀ​መ​ሪያ ፍጥ​ረቱ አዳ​ምን የበ​ለ​ስን ፍሬ በማ​ብ​ላት አሳ​ተ​ችው፤ የፈ​ጣ​ሪ​ዋ​ንም ትእ​ዛዝ ስለ ተላ​ለ​ፈች በእ​ር​ስ​ዋና በል​ጆ​ችዋ ሞትን አመ​ጣች።

7 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እው​ነ​ተኛ ፍርድ ከገ​ነት ወጡ፤ ተጣ​ል​ቶም ከገ​ነት አላ​ራ​ቃ​ቸ​ውም። ነገር ግን በተ​ሰ​ደ​ዱ​በት ምድር በሆ​ዳ​ቸው ፍሬ በል​ጆ​ቻ​ቸ​ውና በም​ድ​ራ​ቸው ፍሬ አረ​ጋ​ጋ​ቸው።

8 በቅ​ን​አ​ት​ህም ከገ​ነት ባስ​ወ​ጣ​ሃ​ቸው ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከገ​ነት የለ​መ​ለሙ ዕፀ​ዋ​ትን ሰጣ​ቸው፤ ይተ​ክሉ ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሰ​ጣ​ቸው በገ​ነት ፍሬና በም​ድር ፍሬ ይረ​ጋጉ ዘንድ፤

9 ልጆ​ችን በማ​የት፥ ገነ​ት​ንና ምድር ከአ​ፈር ያበ​ቀ​ለ​ች​ውን የም​ድር ፍሬ በማ​የት ልቡ​ና​ቸ​ውን እጅግ ደስ ያሰኙ ዘንድ፤ እር​ሱ​ንም በበሉ ጊዜ ከገ​ነት እነ​ር​ሱን ካስ​ወ​ጣ​ህ​በት ኀዘን ፈጽ​መው ይረ​ጋ​ጋሉ።

10 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፍጥ​ረ​ቱን ማረ​ጋ​ጋት ያው​ቃ​ልና በል​ጆ​ቻ​ቸ​ውና በም​ድር ፍሬ ልቡ​ና​ቸው ይረ​ጋ​ጋል።

11 ወደ​ዚች የእ​ሾ​ህና የአ​ሜ​ከላ ምድ​ርም ተሰ​ደ​ዋ​ልና ልቡ​ና​ቸ​ውን በእ​ህ​ልና በውኃ ያጸ​ናሉ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች