Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ሣልስ 2 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 “አንተ ግን እንደ ባር​ያዬ እንደ ኢዮብ ማሳት የተ​ሳ​ነ​ህን እኔ በክ​ብር የአ​ን​ተን ዙፋን አወ​ር​ሳ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ አንተ ማሳት ለተ​ሳ​ነህ ሰዎች መን​ግ​ሥተ ሰማ​ያ​ትን እሰ​ጣ​ቸ​ዋ​ለሁ ይላል ሁሉን የሚ​ችል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።”

2 እኔም የአ​ዳ​ምን ልጆች በሁሉ እተ​ነ​ኰ​ል​ባ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ እነ​ር​ሱን ማሳት ከተ​ቻ​ለኝ በበጎ ሥራ ይጸኑ ዘንድ አል​ተ​ዋ​ቸ​ውም፤ የአ​ዳ​ምን ልጆች ሁሉ እተ​ነ​ኰ​ል​ባ​ቸ​ዋ​ለ​ሁና፥ የዓ​ለ​ምን ምኞ​ትም አጣ​ፍ​ጥ​ላ​ቸ​ዋ​ለ​ሁና።

3 መብ​ልን በመ​ው​ደድ፥ መጠ​ጥ​ንም በመ​ው​ደድ፥ ልብ​ስን በመ​ው​ደ​ድም ቢሆን፥ ነገ​ር​ንም በመ​ው​ደድ፥ በመ​ስ​ጠ​ትም በመ​ን​ሣ​ትም ቢሆን፥

4 መስ​ማ​ት​ንና ማየ​ት​ንም በመ​ው​ደድ ቢሆን፥ መዳ​ሰ​ስ​ንና መሄ​ድ​ንም በመ​ው​ደድ ቢሆን፥ ትዕ​ቢ​ት​ንና ነገ​ር​ንም በማ​ብ​ዛት ቢሆን፥ እን​ቅ​ል​ፍ​ንና ሕል​ም​ንም በመ​ው​ደድ ቢሆን፥

5 መጠ​ጥ​ንና ስካ​ርን በማ​ብ​ዛት ቢሆን፥ ስድ​ብ​ንና ቍጣ​ንም በማ​ብ​ዛት ቢሆን፥ ቡዋ​ል​ት​ንና ቀል​ድን በመ​ና​ገ​ርም ቢሆን፥

6 ባል​ን​ጀ​ራ​ቸ​ው​ንም በማ​ማት በጠብ ቢሆን፥ መልከ መል​ካ​ሞች የሆኑ የዚ​ህን ዓለም ሴቶ​ችን በማ​የ​ትም ቢሆን፥ የሚ​ያ​ስ​ት​ዋ​ቸ​ውን የሽ​ቱ​ዎ​ችን መዓዛ በማ​ሽ​ተ​ትም ቢሆን፥

7 መዳ​ንን እን​ዳ​ይ​ችሉ በዚህ ሁሉ እኔ እጣ​ላ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በእ​ነ​ር​ሱም ምክ​ን​ያት ከመ​ን​በሬ ወደ ተዋ​ረ​ድ​ሁ​በት ጥፋት ከእኔ ጋራ ይገቡ ዘንድ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መን​ገድ አር​ቃ​ቸ​ዋ​ለሁ።

8 ነቢ​ዩም እን​ዲህ አለ፥ “አንተ ጥፉና አጥፊ! በት​ዕ​ቢ​ት​ህና በል​ብህ ደን​ዳ​ና​ነት፥ ፈጣ​ሪ​ህን በማ​ሳ​ዘ​ንና ፈጣ​ሪ​ህ​ንም ባላ​ማ​መ​ስ​ገን አንተ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትእ​ዛዝ ወጥ​ተህ በካ​ድህ ጊዜ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፍጥ​ረት ላይ እን​ዲህ ትታ​በ​ያ​ለ​ህን?

9 ፈጣ​ሪህ በተ​ቈ​ጣህ ጊዜ ስለ ክፉ ሥራህ ጣለህ፤ ፈጣ​ሪው ከመ​ሬ​ትና ከት​ቢያ የፈ​ጠ​ረ​ውን፥ እንደ ወደ​ደም የሠ​ራ​ው​ንና ለም​ስ​ጋ​ናው ያኖ​ረ​ውን ምስ​ኪን ለምን ትወ​ስ​ደ​ዋ​ለህ?

10 “ረቂቅ የም​ት​ሆን አንተ ከእ​ሳት ነበ​ል​ባ​ልና ከነ​ፋስ የፈ​ጠ​ረ​ህን ፈጣሪ ነኝ በማ​ለት በታ​በ​ይህ ጊዜ፥

11 አን​ተም በተ​መ​ካህ ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክፉ ሥራ​ህን ተመ​ለ​ከተ፤ ሳያ​ጓ​ድል ስሙን ያመ​ሰ​ግን ዘንድ፥ በአ​ንተ ፋንታ የሚ​ያ​መ​ሰ​ግን አዳ​ምን ፈጠ​ረው፤ አንተ ከሠ​ራ​ዊ​ቶ​ችህ ጋራ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ክደ​ሃ​ልና።

12 አዳ​ምና ልጆ​ቹም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስለ ትዕ​ቢ​ትህ በና​ቃ​ችሁ በአ​ን​ተና በሠ​ራ​ዊ​ትህ ምስ​ጋና ፋንታ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ስም ያመ​ሰ​ግኑ ዘንድ ተፈ​ጠሩ፤ ከሊ​ቃነ መላ​እ​ክት ሁሉ ይልቅ ራስ​ህን አኵ​ር​ተ​ሃ​ልና።

13 ስለ​ዚ​ህም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ አንተ ከአሉ ከመ​ላ​እ​ክት አለ​ቆች ሁሉ ለይቶ አዋ​ረ​ደህ፤ በአ​ንድ ምክር የተ​ፈ​ጠ​ራ​ችሁ አን​ተና ሠራ​ዊ​ት​ህም ስለ​ማ​ይ​ጠ​ቅም ስለ ልቡ​ና​ችሁ መደ​ን​ደ​ንና ስለ ሕሊ​ና​ችሁ ትዕ​ቢት ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምስ​ጋና ወጥ​ታ​ችሁ ሳታ​ችሁ፤ በሌ​ላም ሳይ​ሆን በፈ​ጣ​ሪ​ያ​ችሁ ላይ ታበ​ያ​ችሁ።

14 ስለ​ዚ​ህም በት​ሑ​ታን ይመ​ሰ​ገን ዘንድ አዳ​ምን ከም​ድር አፈር ፈጠ​ረው፤ ከበ​ለ​ስም ፍሬ እን​ዳ​ይ​በላ ትእ​ዛ​ዝ​ንና ሕግን ሰጠው።

15 በፈ​ጠ​ረ​ውም ሁሉ ላይ ሾመው፤ እን​ዲ​ህም ብሎ አስ​ታ​ወ​ቀው፤ “በገ​ነት ውስጥ ከአ​ለው ዛፍ ሁሉ ብላ፤ በራ​ስ​ህም ላይ ሞትን እን​ዳ​ታ​መጣ የሞት እሾህ ከሆ​ነ​ችው ከአ​ን​ዲት ዛፍ አት​ብላ፤”

16 ይህ​ቺ​ንም ቃል በሰ​ማ​ሃት ጊዜ ከአ​ዳም የጎን አጥ​ንት በተ​ገ​ኘች በሔ​ዋን ላይ የአ​ፍ​ህን መርዝ ተፋህ።

17 እንደ አን​ተም ሕግ አፍ​ራሽ ታደ​ር​ገው ዘንድ በክፉ ሽን​ገላ ንጹ​ሑን በግ ነጠ​ቅ​ኸው።

18 እንደ የዋህ ርግብ ሆና የተ​ፈ​ጠ​ረች ተን​ኰ​ል​ህን የማ​ታ​ውቅ ሔዋ​ን​ንም ባሳ​ት​ሃት ጊዜ በተ​ከ​ና​ወነ ነገ​ር​ህና በጠ​ማማ ቃልህ አስ​ካ​ድ​ሃት፤ ያች​ንም መጀ​መ​ሪ​ያ​ዪ​ቱን ፍጥ​ረት ካሳ​ት​ሃት በኋላ፥ እርሷ ሄዳ ከመ​ሬት የተ​ፈ​ጠረ መጀ​መ​ሪ​ያ​ውን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፍጥ​ረት አዳ​ምን አሳ​ተ​ችው።

19 በት​ዕ​ቢ​ት​ህም ወደ​ማ​ይ​ገባ ሁከት ጨመ​ር​ኸው፤ የፈ​ጣ​ሪ​ው​ንም ቃል እን​ዲ​ክድ አደ​ረ​ግ​ኸው፤ በት​ዕ​ቢ​ት​ህም ድሃ​ውን አጠ​ፋ​ኸው።

20 በተ​ን​ኰ​ል​ህም ከፈ​ጣ​ሪው ፍቅር አራ​ቅ​ኸው፤ በም​ክ​ን​ያ​ት​ህም ከደ​ስታ ገነት አወ​ጣ​ኸው፤ በመ​ሰ​ና​ክ​ል​ህም የገ​ነ​ትን መብል አስ​ተ​ው​ኸው።

21 በሐ​ሰ​ት​ህም ከገ​ነት መጠጥ አስ​ጠ​ማ​ኸው፤ አንተ ፍዳ ወደ​ም​ት​ቀ​በ​ል​ባት ወደ ሲኦል ታወ​ር​ደው ዘንድ ካለ​መ​ኖር ወደ እው​ነ​ተኛ መኖር ካመ​ጣው አም​ላ​ኩም ፍቅር ታወ​ጣው ዘንድ የዋህ አዳ​ምን ከጥ​ንት ጀምሮ አንተ ተጣ​ል​ተ​ኸ​ዋ​ልና።

22 መሬ​ታ​ዊም ሲሆን በነ​ፍ​ሱና በሥ​ጋው፥ በል​ቡ​ና​ውም ፈጣ​ሪ​ውን የሚ​ያ​ከ​ብ​ርና የሚ​ያ​መ​ሰ​ግን መን​ፈ​ሳ​ዊና ተና​ጋሪ አደ​ረ​ገው።

23 እንደ በገና በተ​ለ​ያዩ ብዙ ስል​ቶች የሚ​ያ​መ​ሰ​ግኑ ዐሥር ሕሊ​ና​ትን ፈጠ​ረ​ለት።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች