Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ሣልስ 1 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ግፈ​ኛና አሳች፥ የፈ​ጣ​ሪ​ው​ንም መን​ገድ የሚ​ፃ​ረር ዲያ​ብ​ሎ​ስን ስለ​ሚ​በ​ቀ​ለው በኋላ ዘመን ስለ​ሚ​መ​ጣው ቸርና የዋህ የግ​ብጽ ደሴ​ቶች ደስ ይላ​ቸ​ዋል።

2 እር​ሱም ይበ​ቀ​ለ​ዋል፤ በል​ቡ​ና​ውም ታብ​ዮ​አ​ልና ክብ​ሩን ወደ መሬ​ትና ወደ መዋ​ረድ ይመ​ል​ሳል።

3 እር​ሱም እን​ዲህ አለ፥ “ከእኔ በላይ ማን ነው? ወደ ባሕሩ ጥልቅ እገ​ባ​ለ​ሁና፥ ወደ ሰማ​ይም እወ​ጣ​ለ​ሁና፥ ጥል​ቆ​ች​ንም አያ​ለ​ሁና፥ የአ​ዳ​ም​ንም ልጆች እንደ ወፍ ጫጩት ጨብጬ እይ​ዛ​ቸ​ዋ​ለ​ሁና።

4 ከቀ​ናች ሕገ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አር​ቃ​ቸው ዘንድ በእ​ነ​ርሱ ላይ ምክ​ን​ያት ስለ​ም​ፈ​ጥር የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፈቃድ ባላ​ደ​ረጉ፥ በም​ድር ላይ በሚ​ኖሩ ሰዎች እኔ እበ​ረ​ታ​ታ​ባ​ቸ​ዋ​ለ​ሁና ከእጄ የሚ​ያ​ስ​ጥ​ለኝ የለም።

5 ከእኔ ጋራም ወደ ጥፋት እን​ዲ​ሄዱ ጐጣ​ጕጥ ወደ ሆነ ጎዳና እመ​ል​ሳ​ቸ​ዋ​ለሁ።

6 “ስለ​ዚ​ህም እር​ሱን የወ​ደ​ዱት፥ ሕጉ​ንም የጠ​በቁ ሰዎች እኔን ይጠ​ላሉ፤ ከጌ​ታ​ቸው ተለ​ይ​ተው የሳቱ ሰዎች ግን ወደ እኔ ይመ​ጣሉ፤ እኔ​ንም ይወ​ድ​ዳሉ፤ ቃል ኪዳ​ኔ​ንም ይጠ​ብ​ቃሉ፤ ወደ ፈጣ​ሪ​ያ​ቸው ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ዳ​ይ​መ​ለሱ ልባ​ቸ​ውን አከ​ፋ​ለ​ሁና፥ አሳ​ባ​ቸ​ው​ንም አጠ​ማ​ለ​ሁና እኔ እን​ዳ​ዘ​ዝ​ኋ​ቸው ትእ​ዛ​ዜን ያደ​ር​ጋሉ።

7 የዚ​ህን ዓለም ገን​ዘብ ባሳ​የ​ኋ​ቸ​ውም ጊዜ ከቀ​ናች መን​ገድ ልቡ​ና​ቸ​ውን አስ​ታ​ለሁ፤ መልከ መል​ካም ሴቶ​ች​ንና ቆነ​ጃ​ጅ​ት​ንም ባሳ​የ​ኋ​ቸው ጊዜ በእ​ነ​ዚህ ከቀ​ናች መን​ገድ አር​ቃ​ቸ​ዋ​ለሁ።

8 የሚ​ያ​ን​ፀ​ባ​ርቁ የሕ​ን​ደኬ ዕን​ቆ​ችን፥ ወር​ቅ​ንና ብርን ባሳ​የ​ኋ​ቸው ጊዜ ወደ እኔ ሥራ ይመ​ለሱ ዘንድ በዚ​ህም ከቀ​ና​ችው መን​ገድ አር​ቃ​ቸ​ዋ​ለሁ።

9 ቀጭን ልብ​ስን፥ ነጭ ሐር​ንና ቀይ ሐርን፥ ግም​ጃ​ንና የተ​ልባ እግ​ርን ባሳ​የ​ኋ​ቸው ጊዜ በዚ​ህም ከቀ​ናች መን​ገድ አር​ቃ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ወደ እኔም አሳብ እመ​ል​ሳ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ገን​ዘ​ብን፥ ከብ​ቶ​ች​ንም እንደ አሸዋ አብ​ዝች ባሳ​የ​ሁ​አ​ቸው ጊዜ በዚ​ህም ወደኔ ሥራ እመ​ል​ሳ​ቸ​ዋ​ለሁ።

10 ስለ ሴቶች፥ ስለ ቍጣና ስለ ጠብ፥ የት​ዕ​ቢት ቅና​ትን ባሳ​የ​ኋ​ቸው ጊዜ በዚህ ሁሉ ወደ እኔ መን​ገድ እመ​ል​ሳ​ቸ​ዋ​ለሁ።

11 ምል​ክ​ቶ​ች​ንም ባሳ​የ​ኋ​ቸው ጊዜ በባ​ል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ቸው ልቡና አድ​ራ​ለሁ፤ በል​ቡ​ና​ቸ​ውም እየ​ራሱ የሆነ የም​ል​ክት ነገ​ርን አሳ​ድ​ራ​ለሁ፤ የቃ​ላ​ቸ​ው​ንም ምል​ክት አሳ​ይች አስ​ታ​ቸ​ዋ​ለሁ።

12 ማደ​ሪ​ያ​ዬም ላደ​ረ​ግ​ኋ​ቸው ሰዎች ምል​ክ​ትን አሳ​ያ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በከ​ዋ​ክ​ብት አካ​ሄ​ድም ቢሆን፥ ወይም በደ​መና መው​ጣት፥ ወይም በእ​ሳት ማና​ፋት፥ ወይም በአ​ው​ሬ​ዎ​ችና በወ​ፎች ጩኸት እነ​ርሱ ማደ​ሪ​ያ​ዎች ናቸ​ውና በዚህ ሁሉ በል​ቡ​ና​ቸው ምል​ክ​ቶ​ችን አሳ​ድ​ር​ባ​ቸ​ዋ​ለሁ።

13 እነ​ርሱ ተና​ግ​ረው ለባ​ል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ቸው ምል​ክት ይሰ​ጧ​ቸ​ዋል፤ እኔም ቀድሜ እነ​ዚያ ሟር​ተ​ኞ​ቻ​ቸው እንደ ነገ​ሯ​ቸው ምል​ክት እሆ​ና​ቸ​ዋ​ለሁ።

14 “የመ​ረ​መ​ሯ​ቸው ሰዎች ይስቱ ዘንድ፥ ዋጋ​ንም ይሰ​ጧ​ቸው ዘንድ፥ እንደ ተና​ገ​ሩት የሚ​ደ​ረ​ግ​ላ​ቸው ትን​ቢ​ት​ንም የሚ​ያ​ውቁ፥ ክፉና በጎ​ንም የሚ​ለዩ፥ ሁሉም እንደ ተና​ገሩ የሚ​ሆ​ን​ላ​ቸው፥ እንደ ቃላ​ቸ​ውም የሚ​ደ​ረ​ግ​ላ​ቸው እንደ እገ​ሊ​ትና እንደ እገሌ ዐዋ​ቆች የሉም ብለው ለባ​ል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ቸው ይነ​ግ​ሯ​ቸው ዘንድ የቃ​ላ​ቸ​ውን ምል​ክት አደ​ር​ግ​ላ​ቸ​ዋ​ለሁ።

15 የሚ​ጠፉ፥ በእ​ኔም የሚ​ስቱ ሰዎች ፈጽ​መው ይበዙ ዘንድ፥ የአ​ዳ​ምም ልጆች ከእኔ ጋር ይጠፉ ዘንድ ይህን በተ​ና​ገሩ ጊዜ እኔ ደስ ይለ​ኛል፤ ለበ​ታች አል​ሰ​ግ​ድም በማ​ለቴ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስለ አባ​ታ​ቸው ስለ አዳም ከክ​ብሬ አዋ​ር​ዶ​ኛ​ልና።

16 “እኔም በት​እ​ዛዜ የሚ​ሄዱ ልጆ​ቹን ሁሉ ወደ ጥፋት እወ​ስ​ዳ​ቸ​ዋ​ለሁ” ያሳ​ት​ኋ​ቸው ሰዎች ከእኔ ጋራ በእ​ሳት ውስጥ ይጨ​መሩ ዘንድ ከፈ​ጠ​ረኝ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ኪዳን አለኝ።

17 እኔም ቍጣ​ውን በእኔ ላይ ባበዛ ጊዜ፥ አስ​ረ​ውም ወደ ገሃ​ነ​ምና ወደ ሲኦል ጥልቅ ይጥ​ሉኝ ዘንድ ባዘዘ ጊዜ፥ ጌታ​ዬን ማለ​ድሁ፤ ፈጣ​ሪ​ዬም እን​ዲህ በአ​ዘዘ ጊዜ ተቈ​ጥ​ተ​ኸ​ኛ​ልና በመ​ቅ​ሠ​ፍ​ት​ህም ገሥ​ጸ​ኸ​ኛ​ልና፥ በመ​ዓ​ት​ህም ቀሥ​ፈ​ኸ​ኛ​ልና አቤቱ ጌታዬ በፊ​ትህ አን​ዲት ነገር እና​ገር ዘንድ ፍቀ​ድ​ልኝ ብዬ በፊቱ ማለ​ድሁ።

18 ጌታ​ዬም፦ ተና​ገር እሰ​ማ​ሃ​ለሁ ብሎ መለ​ሰ​ለኝ፥ ያን​ጊ​ዜም ወደ እርሱ እን​ዲህ እያ​ልሁ እለ​ምን ጀመ​ርሁ። ከክ​ብሬ ከተ​ዋ​ረ​ድሁ በኋላ ያሳ​ት​ኋ​ቸው ሰዎች እኔ መከራ በም​ቀ​በ​ል​በት ከእኔ ጋር ይሁኑ።

19 ነገር ግን እንቢ ያሉኝ፥ በእ​ኔም ያል​ሳቱ፥ ትእ​ዛ​ዝ​ህን ያደ​ርጉ ዘንድ፥ ፈቃ​ድ​ህ​ንም ይፈ​ጽሙ ዘንድ፥ ቃል​ህ​ንም ይጠ​ብቁ ዘንድ፥ ትእ​ዛ​ዜን ያል​ጠ​በቁ፥ እኔም እን​ዳ​ስ​ተ​ማ​ር​ኋ​ቸው እንቢ ባሉ ጊዜ፥ እኔም እን​ዳ​ሳ​ት​ኋ​ቸው በእኔ ባል​ሳቱ ጊዜ እነ​ርሱ ለመ​ን​ግ​ሥ​ትህ ይሁኑ፤ ትወ​ድ​ደ​ኝም በነ​በረ ጊዜ ለእኔ የሰ​ጠ​ኸ​ኝን ዘውድ ይው​ሰዱ።

20 ከእኔ ጋር ላል​ተ​ሰ​ደ​ዱና ሰይ​ጣ​ናት ላል​ተ​ባሉ ሥል​ጣ​ና​ትም የእ​ኔን ዘውድ ስጣ​ቸው፤ ከእ​ኔና ከሠ​ራ​ዊ​ቶ​ችም ባዶ በሆ​ነች መን​በሬ በቀ​ኝህ አስ​ቀ​ም​ጣ​ቸው።

21 እንደ ወደ​ድ​ህም ያመ​ስ​ግ​ኑህ፤ እንደ እኔና እንደ ሠራ​ዊ​ቶች ይሁኑ፤ እኔን ጠል​ተህ ከአ​መ​ድና ከመ​ሬት የተ​ፈ​ጠ​ሩ​ትን ስለ ወደ​ድ​ሃ​ቸው፥ የእኔ ሥል​ጣን ተሽ​ሮ​አ​ልና፥ የእ​ነ​ር​ሱም ሥል​ጣን ከፍ ከፍ ብሏ​ልና እንደ ወደ​ድህ ያመ​ስ​ግ​ኑህ።”

22 ጌታ​ዬም መልሶ እን​ዲህ አለኝ፥ “እያ​ዩና እየ​ሰሙ ሥራ​ዬን ሳይ​ወዱ አንተ አስ​ተ​ሃ​ቸ​ዋ​ልና እንደ ፈቃ​ድ​ህና እንደ ቃልህ ይሁ​ኑህ።

23 ትእ​ዛ​ዜ​ንና የመ​ጻ​ፎ​ችን ቃል ትተው ወደ አንተ ከመጡ ጥፋ​ታ​ቸው አያ​ሳ​ዝ​ነ​ኝም፤ አን​ተም ከአ​ሳ​ት​ሃ​ቸው ከአ​ንተ ጋር በገ​ሃ​ነም ይቀጡ።

24 እስከ ዘለ​ዓ​ለሙ ድረስ ለአ​ን​ተና በአ​ንተ ለሳቱ ከገ​ሃ​ነም ቅጣት መውጫ የላ​ች​ሁም። ነገር ግን ለዘ​ለ​ዓ​ለም በእ​ሳት ውስጥ ትሠ​ቃ​ያ​ላ​ችሁ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች