Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 9 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያይ​ደ​ለህ አንተ ደካማ ሰው ሆይ! ለምን ትኰ​ራ​ለህ? ዛሬ ሰው ነህ፤ ነገም መሬ​ትና ዐመድ ነህ፤ በመ​ቃ​ብ​ር​ህም ትልና ብስ​ባሽ ትሆ​ና​ለህ።

2 ዳግ​መ​ኛም አን​ተ​ንና የአ​ን​ተን ሥራ የሚ​ሠ​ሩ​ትን ሲኦል ትከ​ተ​ላ​ቸ​ዋ​ለች፤ የአ​ንተ መም​ህር አባ​ታ​ችን አዳ​ምን ስለ አሳተ የዐ​ለ​ምን ሁሉ ኀጢ​አት ወደ ራሱ የሚ​መ​ልስ ሰብ​ል​ያ​ኖስ ነውና፤

3 ራሱ​ንም በማ​ኵ​ራ​ትና ልቡ​ና​ውን በማ​ደ​ን​ደን ለፈ​ጣ​ሪው ሥራ መስ​ገ​ድን እንቢ ብሏ​ልና።

4 አን​ተም እንደ መም​ህ​ርህ ለፈ​ጣ​ሪህ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መስ​ገ​ድን እንቢ ብለ​ሃል።

5 አን​ተም ፈጣ​ሪ​ያ​ቸው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የማ​ያ​ው​ቁት የቀ​ደ​ሙህ እንደ ሄዱት ትሄ​ዳ​ለህ፤

6 በም​ድር ስለ ሠሩት ስለ ክፉ ሥራ​ቸው እንደ ተበ​ቀ​ላ​ቸ​ውና ወደ ሲኦል እንደ ወረዱ፥

7 አን​ተም እንደ እነ​ርሱ ወደ ገሃ​ነም ትወ​ር​ዳ​ለህ።

8 ቍጣ​ው​ንም አነ​ሣ​ሥ​ተ​ሃ​ልና፥ በአ​ም​ስ​ቱም መን​ግ​ሥ​ታት ላይ ሥል​ጣ​ንን የሰ​ጠህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ማም​ለክ ቸል ብለ​ሃ​ልና፥ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እጅ የም​ታ​መ​ልጥ ይመ​ስ​ል​ሃ​ልን?

9 ፈቃ​ዱ​ንም ታደ​ርግ እንደ ሆነ፥ አታ​ደ​ር​ግም እንደ ሆነ መረ​መ​ረህ፤ በም​ድ​ርም መን​ገ​ድ​ህን ብታ​ሣ​ምር እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መን​ገ​ድ​ህን ያከ​ና​ው​ን​ል​ሃል፤ እጅ​ህ​ንም ያኖ​ር​ህ​በ​ትን ሁሉ ያከ​ና​ው​ን​ል​ሃል፤ ይባ​ር​ክ​ል​ሃ​ልም፤ ጥንተ ጠላ​ቶ​ች​ህ​ንና የዕ​ለት ጠላ​ቶ​ች​ህ​ንም ያስ​ገ​ዛ​ል​ሃል።

10 በመ​ው​ጣ​ት​ህና በመ​ግ​ባ​ትህ፥ በሆ​ድ​ህም ፍሬ፥ በመ​ን​ጋ​ዎ​ች​ህና በድ​ል​ቦ​ች​ህም፥ በጣ​ቶ​ች​ህም በአ​መ​ለ​ከ​ት​ህ​በት ሥራ ሁሉ፥ በል​ብ​ህም ባሰ​ብ​ኸው ሁሉ ደስ ይል​ሃል፤ እን​ዲህ ታደ​ርግ ዘንድ፥ ትሠ​ራና ትተ​ክል፥ ታፈ​ር​ስም ዘንድ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ሥል​ጣን ተሰ​ጥ​ቶ​ሃ​ልና ሁሉ ይታ​ዘ​ዝ​ል​ሃል።

11 ነገር ግን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃልና ሕግ መስ​ማ​ትን እንቢ ብትል፥ በፍ​ር​ዱም ባት​ኖር ፍርዱ ሁሉ እው​ነት ነውና ከአ​ንተ አስ​ቀ​ድሞ እንደ ነበሩ፥ በሚ​ገ​ባም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እን​ደ​ማ​ያ​መ​ል​ኩት፥ በቀና ፍር​ዱም ጸን​ተው እን​ዳ​ላ​መኑ ወን​ጀ​ለ​ኞች ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እጅ የም​ታ​መ​ል​ጥ​በት የለም።

12 ከፊ​ቱም የሚ​ሰ​ወር የለም፤ ነገር ግን ሁሉ በፊቱ ፈጽሞ የተ​ገ​ለጠ ነው።

13 የነ​ገ​ሥ​ታ​ቱን ሥል​ጣን የሚ​ይ​ዝና የኀ​ይ​ለ​ኞ​ችን ዙፋን የሚ​ገ​ለ​ብጥ እርሱ ነው።

14 የተ​ዋ​ረ​ዱ​ት​ንም ከፍ ከፍ የሚ​ያ​ደ​ርግ፥ የወ​ደ​ቁ​ት​ንም የሚ​ያ​ነሣ እርሱ ነው።

15 የታ​ሰ​ሩ​ትን የሚ​ፈታ እርሱ ነው፤ የሞ​ቱ​ት​ንም የሚ​ያ​ስ​ነሣ እርሱ ነው፤ የይ​ቅ​ርታ ጠል ከእ​ርሱ ዘንድ ነውና ሥጋ​ቸው የፈ​ረ​ሰና የበ​ሰ​በሰ፥ እንደ ትቢ​ያም የሆነ ሰዎ​ችን በወ​ደደ ጊዜ ያስ​ነ​ሣ​ቸ​ዋል።

16 አሳ​ዝ​ነ​ው​ታ​ልና ክፉ ሥራ የሠሩ ሰዎ​ች​ንም የደ​ይን ትን​ሣ​ኤን ያስ​ነ​ሣ​ቸ​ዋል፤ ይበ​ቀ​ላ​ቸ​ዋ​ልም።

17 በም​ድ​ርም ዘራ​ቸ​ውን ያጠ​ፋል፤ እነ​ርሱ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሕጉ​ንና ሥር​ዐ​ቱን ያፈ​ረሱ ናቸ​ውና፤

18 የጻ​ድ​ቃን መን​ገድ ከኃ​ጥ​ኣን መን​ገድ ይልቅ ጭንቅ ነውና ኃጥ​ኣን በጻ​ድ​ቃን ምክር ይኖሩ ዘንድ አይ​ወ​ድ​ዱም።

19 ሰማይ ከም​ድር የራቀ እንደ ሆነ እን​ደ​ዚሁ የጻ​ድ​ቃን መን​ገድ ከኀ​ጥ​ኣን መን​ገድ የራቀ ነው።

20 የኃ​ጥ​ኣን መን​ገድ ግን የቅ​ሚ​ያና የክ​ፋት፥ የዐ​መ​ፅና የዝ​ሙት፥ የስ​ስ​ትና የክ​ዳት ነው፤ በዐ​መ​ፅም መስ​ከ​ርና የሰ​ውን ገን​ዘብ መቀ​ማት ነው።

21 የሰ​ውን ደም ወደ ማፍ​ሰስ ፈጥኖ መሔድ፥ በማ​ይ​ጠ​ቅም ጥፋት ማድ​ረግ፥ ድሃ​አ​ደ​ጉን ማስ​ለ​ቀስ፥ ደም​ንና ሞቶ ያደ​ረ​ውን መብ​ላት፥ የግ​መ​ልና የእ​ሪ​ያም ሥጋ መብ​ላት፥ ወደ አራ​ስና ሳት​ነጻ በደሟ ወዳ​ለች ሴት መሔድ ነው።

22 ይህም ሁሉ የኃ​ጥ​ኣን ሥራ ወደ ዘለ​ዓ​ለም ጥፋ​ትና ቅጣት የሚ​ወ​ስድ ሰፊ መን​ገ​ድና የተ​ዘ​ረጋ የሰ​ይ​ጣን ወጥ​መድ ነው።

23 ጠባ​ብና ቀጭን የም​ት​ሆን የጻ​ድ​ቃን ጎዳና ግን ወደ ሕይ​ወት፥ ወደ የዋ​ህ​ነ​ትና ወደ ትሕ​ት​ናም፥ ወደ ፍቅ​ርና ሰላም፥ ወደ ጾምና ጸሎት፥ ወደ ሥጋም ንጽ​ሕና፥ ከማ​ይ​ጠ​ቅም፥ አባላ የተ​መ​ታ​ው​ንና ሞቶ ያደ​ረ​ውን ከመ​ብ​ላት፥ ወደ ጐል​ማሳ ሚስት ከመ​ሔ​ድና ከዝ​ሙ​ትም ወደ መጠ​በቅ የም​ት​ወ​ስድ ናት።

24 ኀጢ​አ​ተ​ኞች ሰዎች ይኸን ሁሉ ያደ​ር​ጋ​ሉና በሕግ ከአ​ል​ታ​ዘዘ ከተ​ጠላ ሥራ ሁሉና ርኩስ መብ​ልን ከመ​ብ​ላት፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከማ​ይ​ወ​ደው ሥራ ሁሉ ይጠ​በ​ቃሉ።

25 ጻድ​ቃን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከማ​ይ​ወ​ደው መን​ገድ ሁሉ ይር​ቃሉ።

26 እር​ሱም ይወ​ድ​ዳ​ቸ​ዋል፤ ከመ​ከ​ራ​ቸ​ውም ሁሉ እንደ አደራ ገን​ዘብ ይጠ​ብ​ቃ​ቸ​ዋል፤ ያድ​ና​ቸ​ዋ​ልም።

27 ኃጥ​ኣ​ንን ግን ሰይ​ጣን ይገ​ዛ​ቸ​ዋል። ሕጉ​ንና ሥር​ዐ​ቱን፥ የሚ​ወ​ደ​ው​ንም ሁሉ ይጠ​ብ​ቃ​ሉና።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች