Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 8 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በት​ዕ​ቢ​ትና በልብ ተን​ኰል ሄደ።

2 በመ​ን​ግ​ሥ​ቱም ዳን​ኤል እን​ዳ​የው ብረት ፅኑ ተብ​ሏ​ልና በዙ​ሪ​ያው ያሉ የአ​ሕ​ዛብ ሀገ​ሮ​ችን ዞረ።

3 በስ​ን​ፍ​ናና በክ​ፋት ሁሉ፥ በሁ​ከ​ትም ይኖ​ራል።

4 ቀድ​ሞም የተ​ና​ገ​ር​ነ​ውን ይሰ​ብ​ራል፥ ያደ​ቅ​ቃል፤ ይበ​ላ​ልም።

5 አን​ገ​ቱን እንደ አደ​ነ​ደነ እንደ አባቱ እንደ ዲያ​ብ​ሎ​ስም መርዝ የሚ​ተፋ ነውና የቀ​ረ​ውን በእ​ግሩ ይረ​ግ​ጣል።

6 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ፈጣ​ሪው እንደ ሆነ አያ​ው​ቀ​ውም፤ ነገር ግን ዘመኔ እንደ ሰማይ ዘመን ሆነ ይላል።

7 በል​ቡ​ና​ውም ፀሐይ ከእ​ርሱ እን​ደ​ሚ​ወጣ ያስ​ባል።

8 በኀ​ይ​ልም ይነ​ሣል፤ በዛ​ብ​ሎን ዕጣ ይሰ​ፍ​ራል፤ በመ​ቄ​ዶ​ን​ያም ሰል​ፍን ያስ​ነ​ሣል፤ ከሰ​ማ​ር​ያም ቀለ​ቡን ይቀ​በ​ላል፤ ከሶ​ር​ያም እጅ መን​ሻን ይሰ​ጡ​ታል።

9 በዘ​ላ​ኖች አው​ራጃ ይሰ​ፍ​ራል፤ እስከ ሲዶ​ናም ይደ​ር​ሳል፤ በአ​ካ​ይ​ያም ግብ​ርን ይጥ​ላል፤ እስከ ፈሳሹ ባሕ​ርም ድረስ አን​ገ​ቱን ከፍ ከፍ ያደ​ር​ጋል፤ ተመ​ል​ሶም እስከ ሕን​ደኬ ባሕር ድረስ መል​እ​ክ​ቱን ይል​ካል።

10 እን​ዲ​ሁም አን​ገ​ቱን እስከ ሰማይ ድረስ ከፍ ከፍ ያደ​ር​ጋል።

11 በመ​ታ​በ​ይና በክ​ፋት ጸንቶ ይኖ​ራል እንጂ ራሱን ማዋ​ረድ የለ​ውም።

12 መን​ገ​ዱም ሁሉ ወደ ጨለ​ማና ወደ ድጥ፥ ወደ ወን​ጀ​ልና ወደ መታ​በ​ይም፥ ደም ወደ ማፍ​ሰ​ስና ወደ መከ​ራም ነው።

13 መን​ገዱ ሁሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ጠ​ላው ነው፤ የቅ​ሚ​ያና የክ​ፋት፥ የኀ​ጢ​አ​ትም መም​ህር ሰብ​ላ​ን​ዮስ እንደ አስ​ተ​ማ​ረው ያደ​ር​ጋል፤ ድሃ​አ​ደ​ጉ​ንም ያስ​ጮ​ሃል፤ ለድ​ሃም አይ​ራ​ራም።

14 የአ​ሕ​ዛ​ብ​ንም ነገ​ሥ​ታት በእጁ አግ​ብቶ ገደ​ላ​ቸው።

15 የጠ​ላ​ቶች አለ​ቆ​ች​ንም ገዛ፤ ብዙ አሕ​ዛ​ብ​ንም ገዛ፤ እንደ ወደ​ደም አስ​ገ​በ​ራ​ቸው።

16 ምሕ​ረ​ትም አላ​ደ​ረ​ገም፤ ከተ​ር​ሴስ ባሕር ጀምሮ እስከ ኢያ​ሪኮ ባሕር ድረስ ያል​ነ​ጠ​ቀው የለም።

17 ለጣ​ዖ​ትም ይሰ​ግድ ነበር፤ ሙቶ ያደ​ረ​ው​ንና ደሙን፥ አባላ የተ​መ​ታ​ው​ንና ለጣ​ዖ​ቶች የተ​ሠ​ዋ​ውን ይበላ ነበር፤ በሥ​ራ​ውም ሁሉ ያለ ፍርድ ፍጹም ቍጣና ክር​ክር ነበር እንጂ ፍርድ አል​ነ​በ​ረ​ውም። ከሥ​ል​ጣኑ በታች ላሉ አሕ​ዛ​ብም የሚ​ያ​ስ​ደ​ነ​ግጥ ሆኗ​ልና እንደ ወደደ ግብ​ርን ያስ​ገ​ብ​ራ​ቸው ነበር።

18 በፊቱ የወ​ደ​ደ​ውን ሁሉ ያደ​ር​ጋ​ልና በፊቱ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መፍ​ራት አል​ነ​በ​ረ​ውም፤ በፈ​ጣ​ሪው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት በተ​ን​ኰል ይኖር ነበር።

19 እንደ ፈጣ​ሪ​ውም አያ​ደ​ር​ገ​ውም ነበር። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ተቈ​ጥቶ በያ​ዘው ጊዜ በባ​ል​ን​ጀ​ራው ላይ ክፉ ነገ​ርን እንደ አደ​ረገ ፍዳ​ውን ይከ​ፍ​ለ​ዋል።

20 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከዚህ ዓለም ስም አጠ​ራ​ራ​ቸ​ውን አጠፋ ዘንድ በት​እ​ዛዜ የማ​ይ​ኖሩ ትዕ​ቢ​ተ​ኞ​ችን እኔ ተበ​ቅዬ አጠ​ፋ​ቸ​ዋ​ለሁ ብሏ​ልና፥ ከእ​ርሱ አስ​ቀ​ድሞ የነ​በሩ ኃጥ​ኣ​ንን እን​ዳ​ጠ​ፋ​ቸው በጊ​ዜው ይበ​ቀ​ለ​ዋል።

21 ክፉ​ዎ​ችም ክፉ እንደ አደ​ረጉ ፍዳ​ቸ​ውን ይቀ​በ​ላሉ።

22 በጎ አድ​ራ​ጊ​ዎ​ችን ግን በጎ​ነት ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ትከ​ተ​ላ​ቸ​ዋ​ለች።

23 ኢያሱ አም​ስ​ቱን የከ​ነ​ዓን ነገ​ሥ​ታ​ትን በአ​ን​ዲት ቀን በአ​ን​ዲት ዋሻ እንደ አጠ​ፋ​ቸው፥ ሠራ​ዊ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም ያጠ​ፋ​ቸው ዘንድ በጸ​ሎቱ ፀሐ​ይን በገ​ባ​ዖን እንደ አቆመ፥ የኤ​ዌ​ዎ​ን​ንና የከ​ና​ኔ​ዎ​ንን፥ የፌ​ር​ዜ​ዎ​ን​ንና የኬ​ጤ​ዎ​ንን፥ የኢ​ያ​ቡ​ሴ​ዎ​ን​ንም ሠራ​ዊት እስ​ኪ​ያ​ጠ​ፋ​ቸው ድረስ ፀሐይ በሰ​ማይ መካ​ከል ቆሟ​ልና በአ​ንድ ጊዜ ሃያ ሺህ ያህል ሰውም እንደ ገደለ፥ እነ​ር​ሱ​ንም እንደ ገደ​ላ​ቸው፥ እግር ከአ​ን​ገ​ትም አድ​ርጎ እንደ አሰ​ራ​ቸው፥ በዋ​ሻም በጦር እንደ ገደ​ላ​ቸው፥ ደን​ጊ​ያም እንደ ገጠ​መ​ባ​ቸው፥

24 በክፉ ሥራ​ቸው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ያ​ሳ​ዝ​ኑ​ት​ንም ሰዎች እን​ደ​ዚህ ያለ መከራ ያገ​ኛ​ቸ​ዋል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች