Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 7 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 የፈ​ጠ​ራ​ችሁ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የማ​ታ​ውቁ፥ ትእ​ዛ​ዙ​ንና ቃሉ​ንም የማ​ት​ጠ​ብቁ አን​ተና እንደ አንተ ያሉት ወዮ​ላ​ችሁ! በሲ​ኦል ጭን​ቅም ተይ​ዛ​ችሁ በተ​ገ​ረ​ፋ​ችሁ ጊዜ በማ​ይ​ረባ ጸጸት ትጸ​ጸቱ ዘንድ አላ​ች​ሁና።

2 ነፍ​ስና ትን​ፋሽ ለሌ​ላ​ቸው፥ ክፉ ነገር ያደ​ረ​ገ​ባ​ቸ​ውን ለማ​ይ​በ​ቀሉ፥ በጎ ነገር ላደ​ረ​ገ​ላ​ቸ​ውም በጎ ነገ​ርን ለማ​ያ​ደ​ርጉ ለጣ​ዖ​ቶ​ችህ እንደ ፈጣ​ሪ​ያ​ችሁ እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የም​ት​ሠ​ዉ​ላ​ቸ​ውና የም​ት​ሰ​ግ​ዱ​ላ​ቸው አን​ተና ካህ​ና​ትህ እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ ከእ​ርሷ መውጫ የላ​ች​ሁም።

3 እና​ን​ተ​ንና የአ​ማ​ል​ክ​ቶ​ቻ​ች​ሁን አገ​ል​ጋ​ዮች፥ እና​ን​ተ​ንም የሚ​ያ​ዝዙ አጋ​ን​ን​ትን ወደ ገሃ​ነመ እሳት ያወ​ር​ዳ​ችሁ ዘንድ እንደ እና​ንተ ያሉ የሰ​ነ​ፎ​ችን ልቡና ለማ​ሳት ሰይ​ጣን በው​ስ​ጣ​ቸው የሚ​ና​ገ​ር​ባ​ቸው የሰው እጅ ሥራ ናቸ​ውና።

4 የሚ​ረ​ባ​ችሁ እን​ደ​ሌለ አታ​ው​ቁ​ምና ትበ​ድ​ላ​ላ​ችሁ፤ ትስ​ታ​ላ​ች​ሁም።

5 ከእ​ና​ን​ተስ ለም​ግ​ባ​ችሁ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የፈ​ጠ​ራ​ቸው እን​ስ​ሳት፥ አው​ሬ​ዎ​ችና ውሾ​ችም ይሻ​ላሉ። እነ​ርሱ ከአ​ን​ዲት ሞት በቀር ዳግ​መኛ ኵነኔ የለ​ባ​ቸ​ው​ምና።

6 እና​ንተ ግን ትሞ​ታ​ላ​ችሁ፤ ዳግ​መ​ኛም እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ መውጫ በሌ​ለ​ባት በገ​ሃ​ነም እን​ቅ​ጥ​ቅጥ ይፈ​ር​ድ​ባ​ች​ኋል።

7 ይኸ​ንም ተና​ግ​ረው ሄዱ፤ ከእ​ር​ሱም ተሰ​ወሩ።

8 ያ ጺሩ​ጻ​ይ​ዳን ግን በጽኑ ፍር​ሀት ተይዞ ሲን​ቀ​ጠ​ቀጥ አደረ፤ እስ​ኪ​ነ​ጋም ድረስ አል​ተ​ወ​ውም።

9 ከዚ​ህም በኋላ የጻ​ድ​ቃ​ንን ሬሳ​ዎች ወደ ጣለ​በት ቦታ ሄደ፤ ነገር ግን አላ​ገ​ኛ​ቸ​ውም፤ ይቀ​ብ​ራ​ቸው ዘንድ ወድ​ዶ​አ​ልና። ነገር ግን ሄዶ ሬሳ​ቸ​ውን እን​ዳ​ይ​ነካ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰው​ሯ​ቸ​ዋ​ልና አጣ​ቸው።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች