Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 4 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በኢ​ያ​ሱም እነ​ር​ሱን ያዳ​ነ​በት ጊዜ አለ።

2 በጌ​ዴ​ዎን እነ​ር​ሱን ያዳ​ነ​በት ጊዜ አለ።

3 በሶ​ም​ሶን፥ በባ​ር​ቅና በዲ​ቦራ፥ በዮ​ዲ​ትም እነ​ር​ሱን ያዳ​ነ​በት ጊዜ አለ፤ በሴ​ትም ቢሆን፥ በወ​ን​ድም ቢሆን አድሮ ከሚ​ያ​ሠ​ቃ​ዩ​አ​ቸው ጠላ​ቶ​ቻ​ቸው እጅ ያድ​ኗ​ቸው ዘንድ መሳ​ፍ​ን​ትን ያስ​ነ​ሣ​ላ​ቸው ነበር።

4 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እንደ ወደደ ከሚ​ያ​ሠ​ቃ​ዩ​አ​ቸው ሰዎች እጅ ያድ​ና​ቸው ነበር።

5 በአ​ደ​ረ​ገ​ላ​ቸ​ውም በጎ ነገር ሁሉ በም​ድ​ራ​ቸው ዘር፥ በም​ድረ በዳ ያለ መን​ጋ​ቸ​ውን ሁሉና ከብ​ታ​ቸ​ው​ንም በማ​ብ​ዛት ደስ ይላ​ቸው ነበር።

6 ከብ​ታ​ቸ​ው​ንና ተክ​ላ​ቸ​ውን ይባ​ር​ክ​ላ​ቸው ነበር፤ በቤ​ትና በም​ድረ በዳ የያ​ዙ​ት​ንም ሁሉ ይባ​ር​ክ​ላ​ቸው ነበር፤ በዐ​ይነ ምሕ​ረት ይመ​ለ​ከ​ታ​ቸው ነበ​ርና እን​ስ​ሶ​ቻ​ቸ​ውን አያ​ሳ​ን​ስ​ባ​ቸ​ውም ነበር፤ የጻ​ድ​ቃን ልጆች ናቸ​ውና ፈጽሞ ይወ​ዳ​ቸው ነበር።

7 እነ​ርሱ ግን በሥ​ራ​ቸው ክፉ በሆኑ ጊዜ በጠ​ላ​ቶ​ቻ​ቸው እጅ አሳ​ልፎ ይሰ​ጣ​ቸው ነበር።

8 በሚ​ያ​ጠ​ፋ​ቸ​ውም ጊዜ ወዲ​ያ​ውኑ ይሹት ነበር፤ ተመ​ል​ሰ​ውም ወደ ፈጣ​ሪ​ያ​ቸው ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይገ​ሠ​ግሡ ነበር።

9 በፍ​ጹም ልቡ​ና​ቸ​ውም በተ​መ​ለሱ ጊዜ ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውን ያስ​ተ​ሰ​ር​ይ​ላ​ቸው ነበር፤ ሥጋና ደም እንደ ሆኑ ያው​ቃ​ቸ​ዋ​ልና የሚ​ያ​ስት የዚህ ዓለም አሳ​ብና፥ አጋ​ን​ን​ትም አሉ​ባ​ቸ​ውና የቀ​ደመ ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውን አያ​ስ​ብ​ባ​ቸ​ውም ነበር።

10 ያ መቃ​ቢስ ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በቅ​ዱሱ ተራራ የሠ​ራ​ውን ይህን ሥር​ዐት በሰማ ጊዜ በን​ስሓ ተጋ​ደለ።

11 ይኸን ነገር ከአ​የና ከሰማ በኋ​ላም በጎ ሥራ መሥ​ራ​ትን አላ​ቃ​ለ​ለም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይቅር ብሎ​አ​ቸ​ዋ​ልና የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች የሚ​ሠ​ሩ​ትን ቸር​ነት ሁሉ መሥ​ራት አላ​ቃ​ለ​ለም፤ ትእ​ዛ​ዙ​ንም ሲተ​ላ​ለፉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሚ​ቀ​ሥ​ፋ​ቸው ጊዜ ያለ​ቅ​ሱና ይጮሁ ነበር፤ ዳግ​መ​ኛም ይቅር ይላ​ቸው ነበር፤ ሕጉ​ንም ይጠ​ብ​ቁት ነበር።

12 መቃ​ቢ​ስም እን​ደ​ዚሁ መን​ገ​ዱን ያቀና ነበር፤ ትእ​ዛ​ዙ​ንም ይጠ​ብቅ ነበር፤ በእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትእ​ዛ​ዝም ይሔድ ነበር።

13 ያን​ጊ​ዜም የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች የሚ​መ​ኩ​በ​ትን ሁሉ ከሰማ በኋላ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ትእ​ዛዝ በመ​ጠ​በቅ እንደ እነ​ርሱ ይመካ ነበር።

14 ቤቱ​ንና ልጆ​ቹ​ንም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግና ትእ​ዛዝ ሁሉ ይሄዱ ዘንድ ይሠ​ራራ ነበር።

15 አይ​ሁድ የሚ​ከ​ለ​ከ​ሉ​ትን ሥር​ዐት እር​ሱም ይከ​ለ​ከል ነበር፤ አይ​ሁ​ድም የሚ​ጠ​ብ​ቁ​ትን ትእ​ዛዝ ሰምቶ ይጠ​ብቅ ነበር፤ እርሱ ልዩ ሞዓ​ባዊ ወገን ሲሆን አይ​ሁድ የሚ​ከ​ለ​ከ​ሉ​ትን ምግ​ብም ይከ​ለ​ከል ነበር።

16 ዐሥ​ራ​ትም ያወጣ ነበር፤ ከበ​ጎ​ቹና ከላ​ሞቹ፥ ከአ​ህ​ዮ​ቹም መጀ​መ​ሪያ የተ​ወ​ለ​ደ​ው​ንና የገ​ዛ​ውን ሁሉ ይሰጥ ነበር፤ እን​ዲ​ሁም አይ​ሁድ የሚ​ሠ​ዉ​ትን መሥ​ዋ​ዕት ፊቱን ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም መልሶ ይሠዋ ነበር።

17 የስ​እ​ለ​ቱ​ንና የኀ​ጢ​አ​ቱን፥ የፈ​ቃ​ዱ​ንና የሰ​ላ​ሙን መሥ​ዋ​ዕ​ትና የዘ​ወ​ት​ሩን መሥ​ዋ​ዕት ይሠዋ ነበር።

18 የአ​ዝ​መ​ራ​ው​ንም መጀ​መ​ሪያ ይሰጥ ነበር፤ አይ​ሁ​ድም የሚ​ያ​ቀ​ር​ቡ​ትን የወ​ይ​ኑን ቍር​ባን ያቀ​ር​ብና ለሾ​መው ለሌ​ዋ​ዊው ይሰጥ ነበር፤ አይ​ሁ​ድም የሚ​ያ​ደ​ር​ጉ​ትን ሁሉ እን​ዲሁ ያደ​ርግ ነበር፤ ዕጣ​ኑ​ንም ያጣ​ፍጥ ነበር።

19 መቅ​ረ​ዝ​ንና ጋኖ​ችን፥ ጠረ​ጴ​ዛ​ዎ​ች​ንና ድን​ኳ​ኖ​ችን፥ አራ​ቱን ኅብ​ርና ቀለ​በ​ቶ​ችን፥ ለቅ​ድ​ስተ ቅዱ​ሳ​ኑም መብ​ራት የተ​ጣራ ዘይ​ትን፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በሚ​ያ​ገ​ለ​ግ​ሉ​በት ጊዜ እስ​ራ​ኤል በቅ​ድ​ስተ ቅዱ​ሳኑ እን​ደ​ሚ​ያ​ደ​ር​ጉት መጋ​ረ​ጃን አሠራ።

20 በሕ​ጉና በሥ​ር​ዐቱ በኖሩ ጊዜ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቸል ብሎ በጠ​ላ​ቶ​ቻ​ቸው እጅ ባል​ጣ​ላ​ቸው ጊዜ፥ መቃ​ቢ​ስም እንደ እነ​ርሱ በመ​ን​ገዱ ሁሉ በጎ ሥራ ይሠራ ነበር።

21 መሪ እን​ዲ​ሆ​ነው፥ ከመ​ረ​ጣ​ቸ​ውና ፈቃ​ዱን ከአ​ደ​ረጉ ከእ​ስ​ራ​ኤል ወገ​ኖ​ችም እን​ዳ​ይ​ለ​የው ሁል​ጊዜ ወደ እስ​ራ​ኤል ፈጣሪ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይጸ​ልይ ነበር።

22 በጽ​ዮን ልጅን፥ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ቤትን ይሰ​ጠው ዘንድ፥ በነ​ቢዩ አን​ደ​በት ከተ​ና​ገ​ረው ከጥ​ፋ​ትም ያድ​ነው ዘንድ ንስሓ በገ​ባ​በ​ትና በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት በአ​ለ​ቀ​ሰው ልቅሶ ሁሉ ንስ​ሓ​ውን ይቀ​በ​ለው ዘንድ፥

23 ዘሩ​ንም ከም​ድር እን​ዳ​ያ​ጠ​ፋ​በት፥ በመ​ግ​ባ​ቱና በመ​ው​ጣ​ቱም ይጠ​ብ​ቀው ዘንድ ዳግ​መኛ ይጸ​ልይ ነበር።

24 በመ​ቃ​ቢስ ሥል​ጣን በታች ከአሉ ከሞ​ዓብ አሕ​ዛ​ብም ያምኑ ዘንድ ደስ አላ​ቸው፤ አለ​ቃ​ቸው በቀ​ናች መን​ገድ ይሄድ ነበ​ርና፥ ፍር​ዱ​ንም ይመ​ለ​ከቱ ነበር፤ ፈቃ​ዱ​ንም ያደ​ርጉ ነበር፤ የአ​ገ​ራ​ቸ​ውን ፍር​ድና ያገ​ራ​ቸ​ውን ቋንቋ ይንቁ ነበ​ርና የመ​ቃ​ቢ​ስም ሥራ እን​ደ​ሚ​ቀ​ናና እን​ደ​ሚ​ሻል ያስ​ተ​ውሉ ነበር።

25 ወደ እር​ሱም መጥ​ተው የመ​ቃ​ቢ​ስን የቸ​ር​ነ​ቱ​ንና የእ​ው​ነ​ቱን ፍርድ ይሰሙ ነበር።

26 ብዙ ገን​ዘ​ብም ነበ​ረው፤ ወን​ዶች ባሮ​ችና ሴቶች ባሮች፥ ግመ​ሎ​ችና አህ​ዮ​ችም ነበ​ሩት፤ ጥሩር የሚ​ለ​ብሱ አም​ስት መቶ ፈረ​ሶ​ችም ነበ​ሩት፤ ኢሎ​ፍ​ላ​ው​ያ​ን​ንና አማ​ሌ​ቃ​ው​ያ​ንን፥ ሶር​ያ​ው​ያ​ን​ንም ፈጽሞ ድል ይነ​ሣ​ቸው ነበር፤ ቀድሞ ጣዖት ሲያ​መ​ልክ ግን ድል ሲነ​ሡት ኖረ።

27 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ከአ​መነ ወዲህ ግን ወደ ሰልፍ ሲሄድ እርሱ ድል ይነሣ ነበር እንጂ እር​ሱን ድል የነ​ሣው አል​ነ​በ​ረም።

28 እነ​ርሱ ግን ይወ​ጉት ዘንድ በጣ​ዖ​ቶ​ቻ​ቸው ኀይል ይመጡ ነበር፤ በጣ​ዖ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ስም ጠር​ተው ይረ​ግ​ሙት ነበር፤ ነገር ግን እም​ነ​ቱን በፈ​ጣ​ሪው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ላይ አድ​ር​ጓ​ልና ድል የሚ​ነ​ሣው አል​ነ​በ​ረም።

29 እን​ዲ​ህም እያ​ደ​ረ​ገና ጠላ​ቶ​ቹ​ንም ድል እየ​ነሣ፥ አሕ​ዛ​ብ​ንም በሥ​ል​ጣኑ እየ​ገዛ ኖረ።

30 ስለ ተበ​ደ​ሉ​ትም ይበ​ቀል ነበር፤ የድ​ሃ​አ​ደ​ጉ​ንም ፍርድ ያጸ​ድቅ ነበር፤

31 ባል​ቴ​ቶ​ች​ንና ድሃ​አ​ደ​ጎ​ች​ንም በች​ግ​ራ​ቸው ጊዜ ይቀ​በ​ላ​ቸው ነበር፤ የተ​ራ​ቡ​ት​ንም ከም​ግብ ያጠ​ግ​ባ​ቸው ነበር፤ የተ​ራ​ቈ​ቱ​ት​ንም ከል​ብሱ ያለ​ብ​ሳ​ቸው ነበር።

32 በጥ​በ​ቡና በእ​ጁም ሥራ ደስ ይለው ነበር፤ ከአ​ለ​ውም ሳይ​ነ​ፍግ ይሰጥ ነበር፤ ለቤተ መቅ​ደ​ስም ዐሥ​ራ​ትን ይሰጥ ነበር፤ መቃ​ቢ​ስም ይኽን እያ​ደ​ረገ ሳለ በመ​ል​ካም ዐረፈ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች