Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 የሞ​ዓብ ሬማት ለሶ​ርያ ቅርብ ናትና ነቢዩ ነገ​ረው።

2 ጕድ​ጓ​ድም ቈፍሮ እስከ አን​ገቱ ገባ፤ መራራ ልቅ​ሶ​ንም አለ​ቀሰ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ስለ ሠራው ኀጢ​አ​ቱም ንስሓ ገባ።

3 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ነቢ​ዩን እን​ዲህ አለው፤ “ከይ​ሁዳ ሀገር ወደ ሬማት ወደ ሞዓቡ ሹም ወደ መቃ​ቢስ ተመ​ለስ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ዲህ ይላል በለው፦ በኀ​ይሌ ጽና​ትና በሠ​ራ​ዊቴ ቅድ​ስ​ቲ​ቱን ከተማ አጠ​ፋ​ኋት እን​ዳ​ትል ከተ​ማ​ዬን ታጠፋ ዘንድ የአ​ንተ ፈጣሪ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በፈ​ቃዴ ላክ​ሁህ እንጂ ይህን ነገር ያደ​ረ​ግ​ኸው አንተ አይ​ደ​ለ​ህም፤

4 በስ​ስ​ትዋ ሁሉ፥ በክ​ዳ​ት​ዋና በሴ​ሰ​ኝ​ነ​ት​ዋም አሳ​ዝ​ና​ኛ​ለ​ችና።

5 እኔም ቸል ብዬ በአ​ንተ እጅ አሳ​ልፌ ሰጠ​ኋት፤ አን​ገ​ት​ህን ስለ አደ​ነ​ደ​ንህ፥ ከተ​ማ​ዪ​ቱ​ንም በእጄ ብር​ታት ከበ​ብ​ኋት ስለ​ም​ትል ስለ አንተ አይ​ደ​ለም። አሁ​ንም ስለ ወለ​ድ​ሃ​ቸው ልጆ​ችህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኀጢ​አ​ት​ህን ይቅር አለህ።

6 አሁ​ንም በፍ​ጹም ልቡ​ናህ ጨክ​ነህ ንስሓ ግባ። የሚ​ጠ​ራ​ጠሩ ሰዎች ንስሓ ለመ​ግ​ባት አይ​ጨ​ክ​ኑ​ምና ተጠ​ራ​ጣሪ አት​ሁን።

7 ነገር ግን በፍ​ጹም ልቡ​ና​ቸው ንስሓ የሚ​ገቡ፥ ስለ ክፋ​ታ​ቸ​ውም ንስሓ በገ​ቡ​በት ሁሉ ወደ ጥመ​ትና ወደ ኀጢ​አት የማ​ይ​መ​ለሱ ሰዎች ብፁ​ዓን ናቸው።

8 በል​ቅ​ሶና በኀ​ዘን፥ በብዙ ልመ​ናና በስ​ግ​ደ​ትም ወደ ፈጠ​ራ​ቸው ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለመ​መ​ለስ የሚ​ጨ​ክ​ኑም ብፁ​ዓን ናቸው፤ ንስሓ የገ​ቡ​ትን ከሳ​ታ​ችሁ በኋላ ንስሓ የገ​ባ​ችሁ እና​ንተ የእኔ ናችሁ ብሏ​ቸ​ዋ​ልና፤

9 ትዕ​ቢ​ተ​ኛ​ው​ንም ከሳተ በኋላ በን​ስሓ ወደ እርሱ በተ​መ​ለሰ ጊዜ ስለ ፍር​ሀ​ት​ህና ስለ ድን​ጋ​ጤህ ኀጢ​አ​ት​ህን ይቅር እል​ሃ​ለሁ አለው፤ የአ​ባ​ትን ኀጢ​አት በል​ጆች ላይ እስከ ሦስ​ተ​ኛና እስከ አራ​ተኛ ትው​ልድ የማ​መጣ፥ ለሚ​ወ​ድ​ዱኝ፥ ሕጌ​ንም ለሚ​ጠ​ብቁ ግን ለእ​ነ​ርሱ እስከ ሺህ ትው​ልድ ድረስ ምሕ​ረ​ትን የማ​ደ​ርግ ፈጣ​ሪህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እኔ ነኝና።

10 አሁ​ንም ስለ ወለ​ድ​ኻ​ቸው ስለ እነ​ዚህ ልጆች ከአ​ንተ ጋራ ያለ​ውን ቃል ኪዳ​ኔን እጠ​ብ​ቃ​ለሁ፤ ስለ ሠራ​ኸው ኀጢ​አ​ት​ህም ያደ​ረ​ግ​ኸ​ውን ንስሓ እቀ​በ​ላ​ለሁ ይላል ሁሉን የሚ​ችል የእ​ስ​ራ​ኤል ቅዱስ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።”

11 ያን​ጊ​ዜም ከጕ​ድ​ጓዱ ወጣ፤ “እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አሳ​ዝ​ኜ​ዋ​ለ​ሁና የወ​ደ​ድ​ኸ​ውን አድ​ር​ገኝ እንጂ ከአ​ንተ እን​ዳ​ል​ለይ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲ​ህና እን​ዲህ ያድ​ር​ገኝ ብሎ ለነ​ቢዩ ሰገደ፤ ለእኛ ሕግ የለ​ን​ምና እንደ አባ​ቶች በት​እ​ዛዙ አል​ሄ​ድ​ሁም፤ አባ​ቶ​ቻ​ች​ንም እን​ዳ​ስ​ተ​ማ​ሩን ጣዖት እን​ደ​ም​ና​መ​ልክ አንተ ታው​ቃ​ለህ።

12 እኔ በኀ​ጢ​አ​ቴና በል​ቡ​ናዬ ትዕ​ቢት የሔ​ድሁ፥ በአ​ን​ገቴ ደን​ዳ​ና​ነ​ትም ፈጣ​ሪ​ዬን ያሳ​ዘ​ንሁ ኀጢ​አ​ተኛ ነኝና። እስከ አሁ​ንም ድረስ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ነቢ​ያት ቃል አል​ሰ​ማ​ሁም ነበር፤ ባዘ​ዘ​ኝም በሕ​ጉና በት​እ​ዛዙ አል​ኖ​ር​ሁም።”

13 ነቢ​ዩም መልሶ፥ “ከእ​ና​ንተ አስ​ቀ​ድሞ ከወ​ገ​ና​ችሁ ኀጢ​አ​ቱን የታ​መነ የለ​ምና ዛሬ ንስ​ሓ​ህን እንደ ተቀ​በለ ዐወ​ቅሁ” አለ።

14 ከእ​ን​ግ​ዲህ ወዲያ ግን ጣዖት ማም​ለ​ክን ተው፤ መመ​ለ​ስህ እው​ነ​ተኛ ይሆን ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ወደ ማወቅ ተመ​ለስ፤ ከነ​ቢ​ዩም እግር በታች ሰገደ፤ ነቢ​ዩም አነ​ሣው፤ የሚ​ገ​ባ​ው​ንም በጎ ሥራ ሁሉ አዘ​ዘው።

15 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ዳ​ዘ​ዘው አደ​ረገ፤ ወደ ቤቱም ተመ​ለሰ።

16 ያም መቃ​ቢስ አእ​ም​ሮ​ውን አስ​ተ​ካ​ከለ፤ ከቤ​ቱም ጣዖ​ቱ​ንና ጥን​ቆ​ላ​ውን፥ ጣዖት የሚ​ያ​መ​ልኩ ሰዎ​ች​ንና ሟር​ተ​ኞ​ችን፥ ጠን​ቋ​ዮ​ች​ንም አስ​ወ​ገደ፤

17 ከኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ያመ​ጣ​ቸ​ው​ንም የም​ርኮ ልጆች አባ​ቶ​ቻ​ቸው እን​ደ​ሚ​ያ​ደ​ርጉ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ትእ​ዛዝ ሁሉ፥ ሥር​ዐ​ቱ​ንና ሕጉ​ንም ያደ​ርጉ እንደ ሆነ ጧትና ማታ ይመ​ረ​ም​ራ​ቸው ነበር።

18 ከተ​ማ​ረ​ኩ​ትም ልጆች ከዐ​ዋ​ቂ​ዎቹ በቤቱ ሾመ።

19 ዳግ​መ​ኛም የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች የሚ​ያ​ደ​ር​ጉ​ትን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሕግ ያስ​ተ​ም​ሯ​ቸው ዘንድ ወደ መኝ​ታው የሚ​ገቡ፥ ታና​ናሽ ቅም​ጥል ልጆ​ቹን የሚ​ጠ​ብቁ ዐዋ​ቂ​ዎ​ችን ከታ​ና​ና​ሾቹ ሾመ፤ ሥር​ዐ​ቱ​ንና ሕጉን፥ አም​ል​ኮ​ቱ​ንና ፍር​ዱን፥ ሞዓ​ባ​ው​ያ​ንም የሚ​ያ​ደ​ር​ጉ​ትን ሥር​ዐት ሁሉ ከም​ርኮ ልጆች ይሰማ ነበር።

20 መስ​ጊ​ዳ​ቸ​ውን፥ ጥን​ቆ​ላ​ቸ​ው​ንና ጣዖ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን፥ ጧትና ማታ ከሰ​ቡት ከፍ​የ​ሎች ጠቦ​ቶ​ችና ከበ​ጎች መን​ጋ​ዎች፥ ለጣ​ዖ​ታቱ የሚ​ሠ​ዋ​ውን መሥ​ዋ​ዕ​ቱ​ንና ወይ​ኑ​ንም ያጠፋ ነበር።

21 በቀ​ት​ርና በሰ​ዓት በሥ​ራው ሁሉ ይሰ​ግ​ድ​ላ​ቸ​ውና ያመ​ል​ካ​ቸው ነበር፤ ይለ​ም​ና​ቸ​ውና ይተ​ማ​መ​ና​ቸ​ውም ነበር፤ እን​ዲ​ሁም ከመ​ን​ገዱ በተ​መ​ለሰ ጊዜ ይለ​ም​ና​ቸው ነበር፤ የጣ​ዖ​ታቱ ካህ​ና​ትም በነ​ገ​ሩት ሁሉ ፈቃ​ዳ​ቸ​ውን ያደ​ርግ ነበር።

22 በነ​ገሩ ሁሉ የሚ​ያ​ድ​ኑት ይመ​ስ​ለው ነበ​ርና የነ​ገ​ሩ​ትን ሁሉ አይ​ን​ቅም ነበር።

23 ያ መቃ​ቢስ ግን የእ​ነ​ር​ሱን መን​ገድ ተወ።

24 ነቢይ የሚ​ሉት የረ​ኣ​ዩን ነገር ከሰማ በኋ​ላም በን​ስሓ መን​ገ​ዱን አሣ​መረ፤ በዚ​ያም ወራት ወገ​ኖቹ ሁሉ ከእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ይልቅ መን​ገ​ዳ​ቸ​ውን አሣ​መሩ፤ የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች አንድ ጊዜ ያሳ​ዝ​ኑት ነበ​ርና በቀ​ሠ​ፋ​ቸ​ውም ጊዜ ዐው​ቀው ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይጮኹ ነበ​ርና።

25 መከራ በሚ​ያ​ጸ​ኑ​ባ​ቸው በአ​ሕ​ዛብ እጅ ተይ​ዘው እንደ ተዋ​ረዱ፥ ወደ እር​ሱም እንደ ጮሁ በሰማ ጊዜ የአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን መሐላ አስቦ የዚ​ያን ጊዜ ስለ አባ​ቶ​ቻ​ቸው ስለ አብ​ር​ሃ​ምና ስለ ይስ​ሐቅ፥ ስለ ያዕ​ቆ​ብም ይቅር ይላ​ቸው ነበር።

26 በአ​ዳ​ና​ቸ​ውም ጊዜ ያዳ​ና​ቸ​ውን ይረ​ሱት ነበር፤ ጣዖ​ታ​ቱ​ንም ወደ ማም​ለክ ይመ​ለሱ ነበር።

27 ያን​ጊ​ዜም በመ​ከራ የሚ​ያ​ሠ​ቃ​ዩ​አ​ቸው አሕ​ዛ​ብን ያስ​ነ​ሣ​ባ​ቸው ነበር፤ በአ​ሠ​ቃ​ዩ​አ​ቸ​ውና ባሳ​ዘ​ኑ​አ​ቸ​ውም ጊዜ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይጮሁ ነበር፤ የዚ​ያን ጊዜም ራርቶ ይቅር ይላ​ቸው ነበር። የእጁ ፍጥ​ረት ስለ ሆኑ ይወ​ድ​ዳ​ቸው ነበ​ርና።

28 ዳግ​መ​ኛም በሚ​ጠ​ብ​ቃ​ቸው ጊዜ በዙ​ሪ​ያ​ቸው ያለ ጣዖ​ትን በማ​ም​ለ​ክና በክ​ፉው የእ​ጃ​ቸው ሥራ ያሳ​ዝ​ኑት ዘንድ ይመ​ለሱ ነበር።

29 እርሱ ግን የኢ​ሎ​ፍ​ሊ​ንና የሞ​ዓ​ብን፥ የም​ድ​ያ​ም​ንና የሶ​ር​ያን፥ የግ​ብ​ፅ​ንም ሕዝብ ያስ​ነ​ሣ​ባ​ቸው ነበር፤ ጠላ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ድል በነ​ሷ​ቸው ጊዜ፥ መከራ በአ​ጸ​ኑ​ባ​ቸ​ውና በአ​ስ​ገ​በ​ሯ​ቸው ጊዜ፥ በገ​ዟ​ቸ​ውም ጊዜ ይጮ​ሁና ያለ​ቅሱ ነበር፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በወ​ደ​ደ​በት ጊዜ ያድ​ኗ​ቸው ዘንድ መሳ​ፍ​ን​ትን ያስ​ነ​ሣ​ላ​ቸው ነበር፤ መሳ​ፍ​ን​ቱም ያድ​ኗ​ቸው ነበር።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች