Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 21 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 የራ​ሳ​ቸው ገን​ዘ​ብና የእ​ጃ​ቸው ሥራ ያል​ሆ​ነ​ውን የሌ​ላ​ውን ገን​ዘብ በዐ​መፅ የሚ​ሰ​በ​ስቡ ሰዎች ወዴት አሉ?

2 ያለ ዋጋ የሌ​ላ​ውን ገን​ዘብ ይወ​ስ​ዳ​ሉና፥ የም​ት​ደ​ር​ስ​ባ​ቸው ዕለተ ሞታ​ቸ​ው​ንም ሳያ​ውቁ ይሰ​በ​ስ​ባ​ሉና፥ ገን​ዘ​ባ​ቸ​ው​ንም ለባ​ዕድ ይተ​ዋ​ሉና።

3 ልጆ​ቻ​ቸ​ውም በአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ገን​ዘብ ደስ አይ​ላ​ቸ​ውም፤ እንደ አባ​ቶ​ቻ​ቸው እንደ እነ​ርሱ ያሉ ኃጥ​ኣ​ንን በስ​ር​ቆ​ትም ቢሆን በቅ​ሚ​ያም ቢሆን፥ አስ​ጨ​ን​ቀው የሚ​ይዙ የኃ​ጥ​ኣን ወገ​ኖች ናቸ​ውና።

4 የአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ገን​ዘብ አይ​ጠ​ቅ​ማ​ቸ​ውም፤ በን​ጥ​ቂ​ያና በግፍ ሰብ​ስ​በ​ው​ላ​ቸ​ዋ​ልና፤ እንደ ጉም ሽን​ትና ነፋስ እን​ደ​ሚ​በ​ት​ነው ጢስም፥ እን​ደ​ሚ​ረ​ግፍ ሣርም፥ በእ​ሳ​ትም ፊት እን​ደ​ሚ​ቀ​ልጥ ሰም እን​ዲሁ የኃ​ጥ​ኣን ክብ​ራ​ቸው ይጠ​ፋል።

5 ዳዊ​ትም እንደ ተና​ገረ፥ “ኀጢ​አ​ተ​ኛን እንደ ሊባ​ኖስ ዛፍ ለም​ል​ሞና ከፍ ከፍ ብሎ አየ​ሁት፤ በተ​መ​ለ​ስሁ ጊዜ ግን አጣ​ሁት፤ ፈለ​ግሁ፤ ቦታ​ው​ንም አላ​ገ​ኘ​ሁም።”

6 የማ​ይ​ሞቱ መስ​ሏ​ቸው የሌ​ላ​ውን ገን​ዘብ በግፍ ስለ​ሚ​ሰ​በ​ስቡ ዛሬ ባል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ቸ​ውን የሚ​በ​ድሉ ሰዎች እን​ዳ​ይ​መኩ የኃ​ጥ​ኣን ጥፋ​ታ​ቸው እን​ደ​ዚህ በአ​ንድ ጊዜ ነው።

7 እና​ንተ ሰነ​ፎች፥ እን​ደ​ም​ታ​ልፉ፥ ገን​ዘ​ባ​ች​ሁም ከእ​ና​ንተ ጋር እን​ደ​ሚ​ያ​ልፍ አስቡ፤ ወር​ቃ​ች​ሁና ብራ​ችሁ ቢበዛ የዛገ ይሆ​ናል።

8 ልጆ​ችን ብታ​በ​ዙም የመ​ቃ​ብር ብዛት ይሆ​ናል፤ ቤቶ​ች​ንም ብታ​በዙ የፈ​ረሰ ይሆ​ናል።

9 የአ​ም​ላ​ካ​ችሁ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፈቃድ አል​ፈ​ጸ​ማ​ች​ሁ​ምና ከብት ብታ​በ​ዙም ለጠ​ላ​ቶ​ቻ​ችሁ ምርኮ ይሆ​ናል፤ ያል​ተ​ባ​ረከ ሆኗ​ልና፥ እጃ​ች​ሁን ያኖ​ራ​ች​ሁ​በት ገን​ዘብ ሁሉ አይ​ገ​ኝም።

10 በቤ​ትም ያለ ቢሆን፥ በዱ​ርም ያለ ቢሆን፥ በመ​ሰ​ማ​ሪ​ያና በእ​ር​ሻም ያለ ቢሆን፥ በእ​ህል አው​ድ​ማና በወ​ይን መጭ​መ​ቂ​ያም ያለ ቢሆን አይ​ገ​ኝም።

11 በሆ​ዳ​ች​ሁም ፍሬ ቢሆን ደስ አይ​ላ​ች​ሁም፤ ነገር ግን ከጠ​ላ​ቶ​ቻ​ችሁ የተ​ነሣ ኀዘን ይሆ​ን​ባ​ች​ኋል። የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ትእ​ዛዝ ስላ​ል​ጠ​በ​ቃ​ችሁ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከቤተ ሰባ​ችሁ ሁሉ ጋር አያ​ድ​ና​ች​ሁ​ምና።

12 ሕጉ​ንና ሥር​ዐ​ቱን፥ ትእ​ዛ​ዙ​ንም የጠ​በቁ ሰዎ​ችን ግን ከበ​ረ​ከቱ አያ​ሳ​ጣ​ቸ​ውም፤ የለ​መ​ኑ​ት​ንም ሁሉ ይሰ​ጣ​ቸ​ዋል፤ የም​ድ​ራ​ቸ​ውን ፍሬና የሆ​ዳ​ቸ​ውን ፍሬም ይባ​ር​ክ​ላ​ቸ​ዋል።

13 እን​ዲ​ገዙ እንጂ እን​ዳ​ይ​ገዙ፥ በዙ​ሪ​ያ​ቸው ከአሉ አሕ​ዛ​ብም ሁሉ በላይ ያደ​ር​ጋ​ቸ​ዋል፤ በመ​ሰ​ም​ሪ​ያ​ቸ​ውም ቦታ በረ​ከ​ቱን ሁሉ ይሰ​ጣ​ቸ​ዋል።

14 እጃ​ቸ​ውን ያኖ​ሩ​በ​ትን ሁሉ፥ የእ​ር​ሻ​ቸ​ውን ፍሬ ሁሉና የከ​ብ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ቦታ ሁሉ ይባ​ር​ክ​ላ​ቸ​ዋል፤ በሆ​ዳ​ቸ​ውም ፍሬ ደስ ያሰ​ኛ​ቸ​ዋል።

15 ከብ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም አያ​ሳ​ን​ስ​ባ​ቸ​ውም፤ ከመ​ከ​ራ​ቸ​ውም ሁሉ ከበ​ሽ​ታና ከድ​ካ​ምም፥ ከጥ​ፋ​ትም፥ ከሚ​ያ​ው​ቁ​ትና ከማ​ያ​ው​ቁ​ትም ያድ​ና​ቸ​ዋል።

16 በፍ​ር​ድም ጊዜ ይከ​ራ​ከ​ር​ላ​ቸ​ዋል፤ ከክፉ ነገ​ርና ከመ​ከ​ራም፥ ከሚ​ቃ​ወ​ማ​ቸ​ውም ሁሉ ያድ​ና​ቸ​ዋል፤ በመ​ጀ​መ​ሪያ የድ​ን​ኳ​ኑን ሥራ በአ​ደራ የተ​ቀ​በለ ሌዋዊ የድ​ን​ኳ​ኑን ሥራ ቢጠ​ብቅ፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፈቃድ ቢሄድ፥ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ሕግ እንደ ሕጉ ሁሉ ዐሥ​ራ​ቱ​ንና ከሰው ጀምሮ እስከ ከብት ድረስ በኵ​ራ​ቱን ይሰ​ጡት ነበር።

17 ሙሴም የነዌ ልጅ ኢያ​ሱን እን​ዳ​ዘ​ዘው በሚ​ፈ​ር​ዱ​በ​ትና ለሚ​ፈ​ር​ዱ​ለት ፍር​ድን እስ​ኪ​ሰጡ ድረስ ባለ​ማ​ወቅ ወይም በማ​ወቅ ነፍስ የገ​ደለ ሰው ቢኖር በዚያ ይድን ዘንድ በከ​ተ​ሞ​ቻ​ቸው ሁሉ መማ​ጸኛ ከተማ ነበር።

18 “ቀድሞ ከእ​ርሱ ጋር ጠብ እን​ዳ​ለው በል​ቡ​ና​ችሁ መር​ምሩ አላ​ቸው፤

19 ምሳ​ርም ቢሆን፥ ድን​ጋ​ይም ቢሆን፥ እን​ጨ​ትም ቢሆን፥ ባለ​ማ​ወቅ ከእጄ ስለ ወደቀ ያ የወ​ደ​ቀ​በት ሰው ሞተ​ብኝ ቢል፥ መር​ም​ራ​ችሁ አድ​ኑት፤ ባለ​ማ​ወቅ አድ​ር​ጎ​ታ​ልና ይድ​ናል።

20 በማ​ወቅ ቢያ​ደ​ር​ገው ግን እንደ በደሉ ፍዳ​ውን ይቀ​በ​ላል፤ የሚ​ም​ረ​ውም የለም፤ ባለ​ማ​ወቅ ቢያ​ደ​ር​ግና ቢገ​ድ​ለው ግን ባለ​ማ​ወቅ አድ​ር​ጎ​ታ​ልና እን​ዳ​ይ​ሞት መር​ም​ራ​ችሁ አድ​ኑት።”

21 ሙሴም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ትእ​ዛዝ እን​ዳ​ይ​ተ​ላ​ለፉ ለእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች እን​ደ​ዚህ ሥር​ዐት ሠር​ቶ​ላ​ቸው ነበር፤ ከክ​ፋ​ትም ሁሉ እን​ዲ​ርቁ ሥር​ዐት ሠር​ቶ​ላ​ቸው ነበር።

22 በፍ​ር​ዱና በሕጉ ይኖሩ ዘንድ፥ ጣዖት ከማ​ማ​ለክ፥ ሙቶ ያደ​ረ​ው​ንና አባላ የተ​መ​ታ​ውን ከመ​ብ​ላ​ትም፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትእ​ዛዝ ለሚ​ኖ​ሩና እንደ ሠራ​ላ​ቸው ከክፉ ሥራ ሁሉ ለሚ​ርቁ ለሰው ልጆች ከማ​ይ​ገ​ባው ሁሉ ፈጽ​መው ይርቁ ዘንድ አዘ​ዛ​ቸው።

23 ነፍ​ሳ​ቸ​ው​ንም ያድኑ ዘንድ፥ በጎ ከሠሩ ከአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ጋራ ማደ​ሪ​ያ​ቸ​ውን ያገኙ ዘንድ በሰ​ማይ ባለች ድን​ኳን አም​ሳል ከሠ​ራ​ላ​ቸው ትእ​ዛዝ እን​ዳ​ይ​ወጡ አዘ​ዛ​ቸው።

24 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ያመ​ኑና በት​እ​ዛዙ የሄ​ዱም እነ​ርሱ የጻ​ድ​ቃን ልጆች ይባ​ላሉ። የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፈቃድ ከአ​ደ​ረጉ ከአ​ዳ​ምና ከሴት ናቸ​ውና።

25 የአ​ዳም ልጆች ነንና፥ በጎ ሥራ​ንና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ደስ የሚ​ያ​ሰ​ኘ​ው​ንም ሁሉ እን​ሠራ ዘንድ በመ​ል​ኩና በም​ሳ​ሌው ፈጥ​ሮ​ና​ልና አይ​ን​ቀ​ንም።

26 በጎ ሥራን ብን​ሠ​ራም በጎ ሥራን ከሠሩ ጋራ መን​ግ​ሥተ ሰማ​ያ​ትን እን​ወ​ር​ሳ​ታ​ለን፤ የሚ​ወ​ዱ​ትን አይ​ለ​ያ​ይ​ምና።

27 በን​ጹሕ የሚ​ለ​ም​ኑ​ትን ሰዎች እጅግ ይወ​ዳ​ቸ​ዋል፤ ጸሎ​ታ​ቸ​ው​ንም ይሰ​ማ​ቸ​ዋል፤ ቈር​ጠው ንስሓ የሚ​ገ​ቡ​ት​ንም ንስ​ሓ​ቸ​ውን ይቀ​በ​ላ​ቸ​ዋል፤ ሕጉ​ንና ሥር​ዐ​ቱን፥ ትእ​ዛ​ዙ​ንም ለሚ​ጠ​ብቁ ሰዎች ኀይ​ል​ንና ጽና​ትን ይሰ​ጣ​ቸ​ዋል።

28 ፈቃ​ዱ​ንም ያደ​ረጉ ሰዎች ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ በመ​ን​ግ​ሥቱ ከእ​ርሱ ጋር ደስ ይላ​ቸ​ዋል፥ ፊተ​ኞ​ችም ቢሆኑ፥ ኋለ​ኞ​ችም ቢሆኑ ምስ​ጋ​ናን ያቀ​ር​ቡ​ለ​ታል። ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘለ​ዓ​ለም አሜን።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች