Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 20 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በፍ​ር​ሀ​ትና በመ​ን​ቀ​ጥ​ቀጥ በፊቱ በቆ​ምን ጊዜ በም​ድር የሠ​ራ​ነው ሥራ​ችን ሁሉ እን​ደ​ማ​ይ​ቀ​ርና እን​ደ​ማ​ይ​ሰ​ወር እመ​ኑኝ።

2 ለመ​ን​ገ​ዳ​ች​ንም ስንቅ ባል​ያ​ዝን ጊዜ፥ ለሰ​ው​ነ​ታ​ች​ንም ልብስ በሌ​ለን ጊዜ፥

3 ለእ​ጃ​ች​ንም ምር​ጕዝ፥ ለእ​ግ​ራ​ች​ንም ጫማ በሌ​ለን ጊዜ፥

4 ድጥም ቢሆን፥ ጐጣ​ጕ​ጥም ቢሆን፥ ጨለ​ማም ቢሆን፥ እሾ​ህም፥ አሜ​ኬ​ላም ቢሆን፥ የባ​ሕር ጥል​ቅም ቢሆን፥ የጕ​ድ​ጓ​ድም ጥልቅ ቢሆን እኛን የሚ​ወ​ስ​ዱ​በ​ትን ጎዳ​ና​ውን በማ​ና​ው​ቅ​በት ጊዜ።

5 የሚ​ወ​ስ​ዱ​ን​ንም አና​ው​ቃ​ቸ​ውም፤ ነገ​ራ​ቸ​ው​ንም አን​ሰ​ማም።

6 እነ​ርሱ ጥቋ​ቍ​ሮች ናቸ​ውና፥ ወደ ጨለ​ማም ይመ​ሩ​ና​ልና፥ ፊታ​ቸ​ውን አና​ይም።

7 ነቢዩ ዳዊት እንደ ተና​ገረ፥ “ነፍሴ በላዬ በአ​ለ​ቀች ጊዜ አቤቱ ጌታዬ ጎዳ​ና​ዬን አንተ ታው​ቃ​ለህ፥ በዚች በሔ​ድ​ሁ​ባ​ትም ጎዳና ወጥ​መድ ሰወ​ሩ​ብኝ፤ ወደ ቀኜም ተመ​ልሼ አየሁ፤ የሚ​ያ​ው​ቀ​ኝም አጣሁ፤ የማ​መ​ል​ጥ​በ​ትም የለ​ኝም።”

8 ይህ​ንም በተ​ና​ገረ ጊዜ፦ አጋ​ን​ንት እን​ደ​ሚ​ዘ​ባ​በ​ቱ​በ​ትና ወደ​ማ​ያ​ው​ቀው ጎዳና እን​ደ​ሚ​መ​ሩት ስለ​ሚ​ያ​ውቅ ነው። ወደ ቀኝና ወደ ግራም ቢመ​ለስ የሚ​ያ​ው​ቀው ሰው አላ​ገ​ኘም።

9 እር​ሱ​ንም የሚ​ያ​ው​ቀው አል​ነ​በ​ረም፤ ነገር ግን በጨ​ለማ መላ​እ​ክት መካ​ከል ነበረ።

10 የጻ​ድ​ቃ​ንን ነፍ​ሳት ይቀ​በሉ ዘንድ፥ ወደ ሕይ​ወት ብር​ሃን ቦታም ይወ​ስዱ ዘንድ ወደ ደጋጉ የሚ​ላኩ ረቂ​ቃን መላ​እ​ክተ ብር​ሃን ናቸው።

11 ይቀ​በ​ሏ​ቸው ዘንድ፥ በሠ​ሩት ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውም ፍዳ​ቸ​ውን ሊቀ​በሉ ወደ ተዘ​ጋ​ጀ​ላ​ቸው ዘለ​ዓ​ለ​ማዊ ቅጣት ይወ​ስ​ዷ​ቸው ዘንድ ወደ ኃጥ​ኣን ነፍ​ሳት የሚ​ላኩ ግን መላ​እ​ክተ ጽል​መ​ትና አጋ​ን​ንት ናቸው።

12 ወደ ጥፋት ለሚ​ወ​ስ​ዷ​ቸው ዕረ​ፍ​ትና ድኅ​ነት ካገ​ኛ​ቸ​ውም መከራ እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ ማም​ለ​ጥና መው​ጣት ለሌ​ላ​ቸው ለኃ​ጥ​አን ነፍ​ሳት ወዮ​ላ​ቸው።

13 በቃ​የን መን​ገድ ሄደ​ዋ​ልና፥ በበ​ለ​ዓ​ምም በደል ዋጋ ጠፍ​ተ​ዋ​ልና፥ የሚ​ያ​ደ​ር​ጉ​ት​ንም አጥ​ተ​ዋ​ልና። ገን​ዘ​ባ​ቸው ያል​ሆ​ነ​ውን የባ​ዕድ ገን​ዘብ በግፍ ይወ​ስዱ ዘንድ መማ​ለ​ጃ​ንና አራ​ጣን ለመ​ቀ​በል ያመ​ካ​ኛ​ሉና።

14 እነ​ር​ሱም እንደ ሠሩት ሥራ​ቸው በገ​ሃ​ነም እሳት ፍዳ​ቸ​ውን ይቀ​በ​ላሉ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች