Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 19 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ምዕ​ራፍ 19

1 ነገ​ሥ​ታ​ት​ንና መኳ​ን​ን​ትን፥ ታላ​ላ​ቆ​ች​ንና ክቡ​ራ​ን​ንም፥ የተ​ዋቡ ሴቶ​ች​ንና መል​ካማ ቆነ​ጃ​ጅ​ት​ንም የሰ​በ​ሰ​ብ​ሻ​ቸው ምድር ሆይ፥ ከአ​ንቺ የተ​ነሣ ወዮ!

2 ደም ግባት ያላ​ቸ​ውን፥ ባተ መል​ካ​ሞች የሆ​ኑ​ትን፥ ዕው​ቀ​ትና ልቡ​ናም ያላ​ቸ​ውን፥ ቃላ​ቸ​ውም እን​ደ​ም​ታ​ን​ጐ​ራ​ጕር በገና፥ እንደ ክራ​ርና እንደ መሰ​ን​ቆም አመ​ታት ያማረ ቃል ያላ​ቸ​ውን፥

3 እንደ ጣፋጭ የወ​ይን መጠ​ጥም ደስ የሚ​ያ​ሰኝ ዜማ ያላ​ቸ​ውን፥ ዐይ​ኖ​ቻ​ቸ​ውም እንደ አጥ​ቢያ ኮከብ የሚ​ያ​በ​ሩ​ትን፥

4 ቀኝ እጃ​ቸ​ውም እን​ደ​ሚ​ሰ​ጥና እን​ደ​ሚ​ነሣ ጽኑዕ የሆ​ነ​ላ​ቸ​ውን፥ የሚ​ነ​ድፉ፥ እግ​ሮ​ቻ​ቸ​ውም ለማ​የት ያማ​ሩና እን​ደ​ተ​ስ​ተ​ካ​ከሉ መን​ኰ​ራ​ኩ​ሮች የሚ​ሮጡ ኀያ​ላን ሰዎ​ችን የሰ​በ​ሰ​ብ​ሻ​ቸው ምድር ሆይ፥ ከአ​ንቺ የተ​ነሣ ወዮ!

5 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፈቃድ ተል​ከ​ሃ​ልና የመ​ልከ መል​ካም ሰዎ​ችን ነፍ​ሳት ከሥ​ጋ​ቸው የለ​የህ ሞት ሆይ! ከአ​ንተ የተ​ነሣ ወዮ!

6 አን​ችም ምድር! እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከአ​ንቺ ያስ​ገ​ኛ​ቸ​ው​ንና ወደ አንቺ የመ​ለ​ሳ​ቸ​ውን ብዙ​ዎች ሥጋ​ዎ​ችን ሰብ​ስ​በ​ሻ​ልና ከአ​ንቺ የተ​ነሣ ወዮ! በፈ​ቃደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከአ​ንቺ ወጣን፤ ወደ አን​ቺም እን​መ​ለ​ሳ​ለን፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፈቃድ በአ​ንቺ ላይ ደስ አለን።

7 ለሬ​ሳ​ዎ​ቻ​ችን ምን​ጣፍ ሆንሽ፤ በላ​ይሽ ተመ​ላ​ለ​ስን፤ በው​ስ​ጥ​ሽም ተኛን፤ ፍሬ​ሽን በላን፤ አን​ቺም ሥጋ​ች​ንን በላሽ።

8 ከም​ን​ጭ​ሽም ውኃ ጠጣን፤ አን​ቺም ከደ​ማ​ችን ምንጭ ጠጣሽ፤ ከመ​ሬ​ትሽ ስባት በላን፤ አን​ቺም የአ​ጥ​ን​ቶ​ቻ​ች​ንን ስባት በላሽ።

9 ምግ​ባ​ችን ልት​ሆኝ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዳ​ዘ​ዘሽ ያማረ ጠል ከአ​ለው ከመ​ሬ​ትሽ እህ​ልን በላን፤ አን​ቺም የሥ​ጋ​ች​ንን ደም ግባት ተቀ​በ​ልሽ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ዳ​ዘ​ዘሽ ለም​ግ​ብሽ ትቢ​ያን አደ​ረ​ግ​ሽው።

10 ብዙ​ዎች ኀያ​ላን ነገ​ሥ​ታ​ት​ንና መኳ​ን​ን​ትን የሰ​በ​ሰ​ብህ፥ የፈ​ጠ​ራ​ቸው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ዳ​ዘ​ዘህ ከገ​ና​ና​ነ​ታ​ቸ​ውና ከግ​ር​ማ​ቸው የተ​ነሣ ያል​ፈ​ራህ፥ ጦም አዳ​ሪ​ው​ንም ያል​ና​ቅህ ሞት ሆይ! ከአ​ንተ የተ​ነሣ ወዮ!

11 መል​ካ​ቸ​ውም ለአ​ማረ ሰዎች አል​ራ​ራ​ህም፤ ኀይ​ለ​ኞ​ች​ንና አር​በ​ኞ​ች​ንም አል​ተ​ው​ህም፤ ባለ​ጸ​ጎ​ች​ንና ድሆ​ችን፥ መልከ ክፉ​ዎ​ች​ንና መልከ መል​ካ​ሞ​ችን፥ ሽማ​ግ​ሌ​ዎ​ች​ንና ልጆ​ችን፥ ሴቶ​ች​ንና ወን​ዶ​ች​ንም አል​ተ​ው​ህም።

12 በጎ የሚ​ያ​ስ​ቡ​ት​ንና ከት​እ​ዛዙ ያል​ተ​ላ​ለ​ፉ​ት​ንም አል​ተ​ው​ህም፤ በሥ​ራ​ቸ​ውም እንደ እን​ስሳ የሆኑ ክፉ ነገር የሚ​ያ​ስ​ቡ​ት​ንም አል​ተ​ው​ህም። በመ​ል​ካ​ቸው ደም ግባት፥ በቃ​ላ​ቸ​ውና በነ​ገ​ራ​ቸው ጣዕም ፍጹ​ማን የሆ​ኑ​ትን አል​ተ​ው​ህም።

13 ቃላ​ቸው ቁጡ የሆ​ነና አፋ​ቸ​ውም ርግ​ማ​ንን የተ​መላ ሰዎ​ችን አል​ተ​ው​ህም፤ ነፍ​ሶ​ቻ​ቸ​ው​ንም በብ​ር​ሃ​ንና በጨ​ለማ መዛ​ግ​ብ​ትህ ሰበ​ሰ​ብህ።

14 ምድ​ርም መለ​ከት እስ​ከ​ሚ​ነ​ፋ​በ​ትና ሙታን እስ​ከ​ሚ​ነ​ሡ​በት ጊዜ ድረስ በዋ​ሻም ቢሆን፥ በመ​ሬ​ትም ቢሆን ሥጋ​ቸ​ውን ሰበ​ሰ​በች።

15 ክፉ አድ​ራ​ጊ​ዎች እንደ ሠሩት ሥራ​ቸው ዋጋ​ቸ​ውን ይቀ​በ​ላሉ፤ በመ​ለ​ከት ድም​ፅና በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትእ​ዛዝ ሙታን እንደ ዐይን ጥቅሻ ይነ​ሣ​ሉና፥ በጎ ሥራ የሠ​ሩም ደስ ይላ​ቸ​ዋል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች