Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 18 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 የሙ​ታ​ንን መነ​ሣት የማ​ታ​ምኑ ሰዎች፥ ምን ያህል ስሕ​ተ​ትን ትስ​ታ​ላ​ችሁ? ወደ​ማ​ታ​ው​ቁ​ትም ቦታ በወ​ሰ​ዷ​ችሁ ጊዜ፥ በነ​ፍ​ስና በሥጋ በአ​ን​ድ​ነት የሙ​ታ​ንን መነ​ሣት ስለ አላ​መ​ና​ችሁ ወደ ገሃ​ነም በጣ​ሏ​ችሁ ጊዜ ያን​ጊዜ የማ​ይ​ረባ ጸጸ​ትን ትጸ​ጸ​ታ​ላ​ችሁ።

2 ትቢ​ያና ዐመድ የሆኑ ሙታን እን​ደ​ማ​ይ​ነሡ እኛ እና​ው​ቃ​ለን እያ​ላ​ችሁ የባ​ል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ች​ሁን ልቡና ታስ​ታ​ላ​ች​ሁና በጎ​ው​ንም ቢሆን፥ ክፉ​ው​ንም ቢሆን እንደ ሠራ​ችሁ ዋጋ​ች​ሁን ትቀ​በ​ላ​ላ​ችሁ።

3 ስለ​ዚ​ህም ባል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ቸ​ውን ያስ​ታሉ፤ ለሞ​ታ​ቸው ዕረ​ፍት የለ​ው​ምና፥ ለመ​ቅ​ሠ​ፍ​ታ​ቸ​ውም ኀይል የለ​ው​ምና፥ በድ​ካ​ማ​ቸ​ውም የጸኑ አል​ሆ​ኑ​ምና፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አደ​ባ​ባ​ይም ይቆሙ ዘንድ አላ​ቸ​ውና።

4 በመ​ዓ​ቱም በሚ​ገ​ሥ​ጻ​ቸው ጊዜ፥ ክፉም ስለ አደ​ረጉ በሚ​ቈ​ጣ​ቸው ጊዜ እጅግ ያፍ​ራሉ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መን​ገድ ሳያ​ውቁ ይና​ገ​ራ​ሉና። ከየት እንደ መጡም አያ​ው​ቁ​ምና።

5 የሚ​ሄ​ዱ​በ​ት​ንም ገሃ​ነም አያ​ው​ቁም፤ ቍጡ​ዎች፥ በሥ​ራ​ቸ​ውም ጠማ​ሞ​ችና ክፉ​ዎች ስለ ሆኑ እንደ ልቡ​ና​ቸው ጥመት ለባ​ል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ቸው ያስ​ተ​ም​ራ​ሉና፤ ትን​ሣኤ ሙታ​ንም የለም እያሉ ጠማማ ነገ​ርን የሚ​ያ​ስ​ተ​ምሩ ናቸ​ውና።

6 ያን​ጊ​ዜም ሙታን እን​ደ​ሚ​ነሡ ያው​ቃሉ፤ ለሰው ልጆች ወገን ሁሉ የሚ​ሆ​ነ​ውን የሙ​ታን ትን​ሣኤ ስለ አላ​መኑ እን​ደ​ሚ​ፈ​ረ​ድ​ባ​ቸው ያው​ቃሉ።

7 ሁላ​ችን የአ​ዳም ልጆች ስለ ሆንን በአ​ዳ​ምም ምክ​ን​ያት ሞተ​ና​ልና፥ ሁላ​ች​ንም በአ​ባ​ታ​ችን በአ​ዳም ስሕ​ተት ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ የሞት ፍርድ አግ​ኝ​ቶ​ና​ልና።

8 ዳግ​መ​ኛም በሠ​ራ​ነው ሥራ​ችን ፍዳ​ች​ንን እን​ቀ​በል ዘንድ ከዚያ ከአ​ባ​ታ​ችን ከአ​ዳም ጋራ እን​ነ​ሣ​ለን፤ በአ​ባ​ታ​ችን በአ​ዳም አለ​ማ​ወቅ ዓለም ለሞት ተገ​ዝ​ት​ዋ​ልና።

9 ስለ​ዚ​ህም በአ​ዳም መተ​ላ​ለፍ ፍዳን እን​ቀ​በ​ላ​ለን፤ ሥጋ​ች​ንም በመ​ቃ​ብር ውስጥ ቀለ​ጠች፤ አጥ​ን​ቶ​ቻ​ች​ንም ደቀቁ።

10 ምድ​ርም ቅል​ጥ​ማ​ች​ንን ጠጣች፤ ጠፋ​ንም፤ ደም ግባ​ታ​ች​ንም በት​ቢያ ጠፋ፤ ሥጋ​ች​ንም በመ​ቃ​ብር ተቀ​በረ፤ የአ​ማረ ቃላ​ች​ንም በመ​ሬት ተቀ​በረ።

11 ከሚ​ያ​በሩ ዐይ​ኖ​ቻ​ች​ንም ትሉ ወጣ፤ መል​ካ​ች​ንም በመ​ቃ​ብር ጠፋ፤ ትቢ​ያም ሆንን።

12 መልከ መል​ካም የነ​በሩ፥ ቁመ​ታ​ቸ​ውም ያማረ፥ የቃ​ላ​ቸ​ውም ንግ​ግር የተ​ቀ​ላ​ጠፈ የጐ​ል​ማ​ሶች የመ​ል​ካ​ቸው ደም ግባት ወዴት አለ? የአ​ር​በ​ኞ​ችስ ገና​ና​ነ​ታ​ቸው ወዴት አለ?

13 የነ​ገ​ሥ​ታቱ ኀይ​ላ​ቸው፥ የመ​ኳ​ን​ን​ቱስ ክብ​ራ​ቸው ወዴት አለ? በፈ​ረስ መጠ​ረር፥ በወ​ር​ቅና በብ​ርም ማጌጥ፥ በሚ​ያ​ን​ጸ​ባ​ርቅ የጦር መሣ​ሪ​ያም መጠ​ረር ወዴት አለ?

14 የመ​ባ​ል​ዕት ጣዕ​ምና ጣፋጩ የወ​ይን መጠጥ የት አለ?

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች