Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 17 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 የስ​ንዴ ቅን​ጣት ካል​ፈ​ረ​ሰች አት​በ​ቅ​ልም፤ ፍሬም አታ​ፈ​ራም። የስ​ንዴ ቅን​ጣት ብት​ፈ​ርስ ግን ወደ ምድር ሥር ትሰ​ዳ​ለች፤ ቅጠ​ልም ታወ​ጣ​ለች፤ ዝር​ዝ​ርም ይሆ​ናል፤ ፍሬም ያፈ​ራል።

2 አን​ዲቱ የስ​ንዴ ቅን​ጣት ብዙ ቅን​ጣት እን​ደ​ም​ት​ሆን እና​ንተ ታው​ቃ​ላ​ችሁ።

3 እን​ደ​ዚሁ ይህች ቅን​ጣት ከነ​ፋ​ስና ከውኃ፥ ከመ​ሬ​ትም የተ​ነሣ ትበ​ቅ​ላ​ለች፥ ፀሐይ ግን በእ​ሳት ፋንታ ነው። ስንዴ ያለ ፀሐይ ፍሬ ማፍ​ራት አይ​ች​ል​ምና።

4 ነፋ​ስም ስለ ነፍስ ፋንታ ነው፥ ያለ ነፋ​ስም ስንዴ ማፍ​ራት አይ​ች​ልም፤ ውኃ​ውም ምድ​ርን ያጠ​ጣ​ታል፤ ያረ​ካ​ታ​ልም።

5 መሬ​ትም ውኃን ከጠ​ጣች በኋላ ሥርን ታስ​ገ​ኛ​ለች፤ ጫፏም ወደ ላይ ከፍ ከፍ ትላ​ለች፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የባ​ረ​ካ​ትን ያህል ታፈ​ራ​ለች።

6 የስ​ንዴ ቅን​ጣት ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የፈ​ጠ​ራት ነባ​ቢት ነፍስ ያደ​ረ​ች​በት የአ​ዳም አም​ሳል ነው፤ የወ​ይን ግን​ድም እን​ደ​ዚሁ ውኃ ይጠ​ጣል፤ ሥርም ይሰ​ድ​ዳል፤ ቀጫ​ጭኑ የሥሩ ገመ​ድም ውኃን ይስ​ባል።

7 ውኃ​ዋ​ንም ወደ ቅጠ​ሎች ጫፍ ያወ​ጣ​ታል፤ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​ገኘ ጠል ረጃ​ጅም የሐ​ረ​ጎ​ችን ጫፎች ያጠ​ጣ​ቸ​ዋ​ልና። በፀ​ሐ​ይም ሙቀት ይዘ​ረ​ዝ​ራል፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፈቃድ ፍሬን ያፈ​ራል።

8 ልብን ደስ የሚ​ያ​ሰኝ በጎ መዓ​ዛ​ንም ያደ​ር​ጋል፤ በበ​ሉ​ትም ጊዜ እን​ደ​ማ​ያ​ስ​ርብ እህ​ልና እን​ደ​ማ​ያ​ስ​ጠማ ውኃ ያጠ​ግ​ባል፤ በጠ​መ​ቁ​ትም ጊዜ የወ​ይን ጠጅ ይሆ​ናል።

9 በጠ​ጡ​ትም ጊዜ “ወይን የሰ​ውን ልብ ደስ ያሰ​ኛል” ተብሎ በመ​ዝ​ሙር እንደ ተነ​ገረ የሰ​ውን ልብ ደስ ያሰ​ኛል፤ ፈታ ፈታ ያለ ሰውም አፉን ከፍቶ በጠጣ ጊዜ ይሰ​ክ​ራል፤ በሳ​ም​ባ​ውም ይመ​ላል፤ ደሙም ወደ ልቡ ይፈ​ስ​ሳል።

10 የወ​ይን ስካር እጅግ ያስ​ታ​ልና አእ​ም​ሮ​ውን ያሳ​ጣ​ዋል፤ ጐጻ​ጕ​ጹ​ንና ገደ​ሉ​ንም እንደ ሰፊ ሜዳ ያደ​ር​ገ​ዋል፤ በእ​ጁና በእ​ግሩ ያለ​ው​ንም እን​ቅ​ፋ​ትና እሾህ አያ​ው​ቅም።

11 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፈቃ​ዱን በሚ​ያ​ደ​ር​ጉና የሙ​ታ​ንን ትን​ሣኤ በሚ​ያ​ምኑ ስሙ ይመ​ሰ​ገን ዘንድ በወ​ይን ግን​ድና በፍ​ሬዋ እን​ዲሁ አደ​ረገ።

12 የሙ​ታ​ንን መነ​ሣት የሚ​ያ​ም​ኑ​ት​ንም በሕ​ይ​ወት ማደ​ሪያ ደስ ያሰ​ኛ​ቸ​ዋል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች