Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 16 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በሥ​ጋህ፥ በእ​ጅ​ህና በእ​ግ​ርህ ጥፍር፥ በራ​ስ​ህም ጠጕር ያለ​ውን እስኪ አንተ ራስህ አስ​በው፤ በቈ​ረ​ጥ​ሃ​ቸው ጊዜ ፈጥ​ነው ይወ​ጣ​ሉና፥ ለማ​መን ልብና አእ​ምሮ ከአ​ለህ በዚህ ዕወቅ።

2 እነ​ዚህ የእ​ጅ​ህና የእ​ግ​ርህ ጥፍር፥ የራ​ስም ጠጕር ከወ​ዴት ይወ​ጣሉ ትላ​ለህ? ከሞት እን​ደ​ም​ት​ነሣ ታውቅ ዘንድ በሌላ ሥጋ ያይ​ደለ በአ​ንተ ሥጋ የሚ​ደ​ረግ ትን​ሣ​ኤን እን​ድ​ታ​ውቅ ይበ​ቅሉ ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያዘ​ጋ​ጀው አይ​ደ​ለ​ምን?

3 አን​ተም የሙ​ታን ትን​ሣኤ የለም እያ​ልህ ሕዝ​ቡን ስለ​አ​ሳ​ትህ ኀጢ​አ​ት​ንና በደ​ልን እንደ ሠራህ በሙ​ታን ትን​ሣኤ ጊዜ ፍዳ​ህን ትቀ​በ​ላ​ለህ።

4 አሁ​ንም የፍ​ዳህ ቀን በደ​ረ​ሰ​ች​ብህ ጊዜ ታያ​ታ​ለህ፤ ስን​ዴም ቢሆን፥ ገብ​ስም ቢሆን አንተ ስንኳ የዘ​ራ​ኸው ይበ​ቅል ዘንድ እንቢ አይ​ል​ምና።

5 ዳግ​መ​ኛም አንተ የተ​ከ​ል​ኸው ተክል አል​በ​ቅ​ልም አይ​ልም፤ የወ​ይን ተክ​ልም ቢሆን፥ የበ​ለስ ተክ​ልም ቢሆን ቅጠ​ሉና ፍሬው አይ​ለ​ወ​ጥም።

6 ወይን ብት​ተ​ክ​ልም በለስ ይሆን ዘንድ አይ​ለ​ወ​ጥም፤ በለ​ስም ብት​ተ​ክል ወይን ይሆን ዘንድ አይ​ለ​ወ​ጥም፤ ስን​ዴም ብት​ዘራ ገብስ ይሆን ዘንድ አይ​ለ​ወ​ጥም፤

7 ገብ​ስም ብት​ዘራ ስንዴ ይሆን ዘንድ አይ​ለ​ወ​ጥም። ነገር ግን ሁሉ በየ​ዘ​ሩና በየ​ወ​ገኑ፥ በየ​ፍ​ሬ​ውና በየ​እ​ን​ጨቱ፥ በየ​ቅ​ጠ​ሉና በየ​ሥሩ፥ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሚ​ገኝ የም​ሕ​ረት ጠል በረ​ከ​ትን ተቀ​ብሎ ፍሬን ያወ​ጣል።

8 እን​ደ​ዚ​ሁም ምድር እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ዘራ​ባት ነፍ​ስ​ንና ሥጋን ታስ​ገ​ኛ​ለች፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የዘ​ራ​ቸው ሥጋና ነፍስ ተዋ​ሕ​ደው ይነ​ሣሉ እንጂ በጎ ሥራ የሠሩ ሰዎች ክፉ ሥራ በሠሩ ሰዎች አይ​ለ​ወ​ጡም፤ ክፉ ሥራም የሠሩ ሰዎች በጎ ሥራን በሠሩ ሰዎች አይ​ለ​ወ​ጡም።

9 መለ​ከት የሚ​ነ​ፋ​በ​ትም ሰዓት በደ​ረሰ ጊዜ ሙታን ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሚ​ገኝ የጠል ምሕ​ረት ይነ​ሣሉ፤ በጎ ሥራ የሠሩ ሰዎች የሕ​ይ​ወት ትን​ሣ​ኤን ይነ​ሣሉ፤ ዋጋ​ቸ​ውም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለደ​ጋ​ጎች ያዘ​ጋ​ጀው፥ መከ​ራና ደዌ የሌ​ለ​በት፥ ከዚ​ህም በኋላ ዳግ​መኛ የማ​ይ​ሞ​ቱ​በት የን​ጹ​ሓን ማደ​ሪያ የደ​ስታ ገነት ነው።

10 ክፉ ሥራ የሠሩ ግን የደ​ይን ትን​ሣኤ ተነ​ሥ​ተው ከአ​ሳ​ታ​ቸው ከዲ​ያ​ብ​ሎስ ጋራ፥

11 ከሰው ልጆች ሁሉ አንድ ሰው ስንኳ ይድን ዘንድ ከማ​ይ​ወዱ ከሠ​ራ​ዊ​ቶቹ ከአ​ጋ​ን​ን​ትም ጋራ ወደ ዘለ​ዓ​ለም ቅጣት ይሄ​ዳሉ፤

12 የጨ​ለማ ዳርቻ ወደ ሆነ፥ ጥርስ ማፋ​ጨ​ትና ልቅሶ ወዳ​ለ​በት፥ ይቅ​ር​ታና ምሕ​ረት ወደ​ሌ​ለ​በት፥ እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ መውጫ ወደ​ሌ​ለ​በት ወደ ገሃ​ነም ይወ​ር​ዳሉ። በሥ​ጋ​ቸው ሳሉ በም​ድር ላይ በሕ​ይ​ወ​ታ​ቸው በጎ ሥራ አል​ሠ​ሩ​ምና።

13 ስለ​ዚ​ህም ነፍ​ስና ሥጋ በት​ን​ሣኤ ጊዜ ይፈ​ረ​ድ​ባ​ቸ​ዋል።

14 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​አ​ም​ራ​ቱን ብዛት የሚ​ያ​ሳ​ይ​ባት የነ​ፍ​ስና የሥ​ጋን በአ​ን​ድ​ነት መነ​ሣት ለማ​ያ​ምኑ ሰዎች ወዮ​ላ​ቸው!

15 ሁሉም እያ​ን​ዳ​ንዱ እንደ ሥራ​ውና እንደ እጁ ድካም ዋጋ​ውን ይቀ​በ​ላል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች