Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 15 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 በጎ ሥራ​ቸ​ውን ያገኙ ያን​ጊዜ ደስ ይላ​ቸ​ዋል፤ ሙታን አይ​ነ​ሡም እያሉ ቸል ያሉ ግን ሙታን ከማ​ይ​ጠ​ቅም ክፉ ሥራ​ቸው ጋራ እንደ ተነሡ በአዩ ጊዜ ያን​ጊዜ ያዝ​ናሉ።

2 ያም የሠ​ሩት ሥራ​ቸው ይፈ​ር​ድ​ባ​ቸ​ዋል፤ የሚ​ከ​ራ​ከ​ራ​ቸ​ውም ሳይ​ኖር እን​ደ​ሚ​ፈ​ረ​ድ​ባ​ቸው እነ​ርሱ ራሳ​ቸው ያው​ቃሉ።

3 በል​ቅ​ሶና በፍ​ርድ ቀን በቍ​ርጥ ፍርድ ቀንና በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቀን ዝን​ጉ​ዎች በሚ​ቆ​ሙ​በት ቦታ ይቆ​ማሉ።

4 በፍ​ጹም ጨለማ ቀን፥ በጉም ቀን፥ በብ​ል​ጭ​ል​ጭታ ቀን፥ በመ​ብ​ረቅ ቀን፥

5 በፍ​ር​ሀ​ትና በመ​ን​ቀ​ጥ​ቀጥ ቀን፥ በብ​ር​ድና በሙ​ቀት ቀን፥ በው​ር​ጭም ቀን፥

6 ክፉ ሰው ክፋ​ትን እንደ ሠራ ፍዳን በሚ​ቀ​በ​ል​ባት ቀን፥ ንጹሕ ሰውም ንጹሕ ሥራን እንደ ሠራ ዋጋ​ውን በሚ​ቀ​በ​ል​ባት ቀን፥ ኀጢ​አ​ተ​ኛም ኀጢ​አ​ትን እንደ ሠራ ፍዳ​ውን እን​ደ​ሚ​ቀ​በል፥

7 ጌታም ከባ​ር​ያው በማ​ይ​ከ​ብ​ር​ባት ቀን፥ እመ​ቤ​ትም ከባ​ር​ያዋ በማ​ት​ከ​ብ​ር​በት ጊዜ፥

8 ንጉ​ሡም ከድ​ሃው በማ​ይ​ከ​ብ​ር​በት ጊዜ፥ ሽማ​ግ​ሌ​ውም ከሕ​ፃኑ በማ​ይ​ከ​ብ​ር​በት ጊዜ፥ አባት ከልጁ በማ​ይ​ከ​ብ​ር​በት ጊዜ፥ እና​ትም ከል​ጅዋ በማ​ት​ከ​ብ​ር​በት ጊዜ፥

9 ባለ​ጸ​ጋው ከድ​ሃው በማ​ይ​ከ​ብ​ር​በት ጊዜ፥ ትዕ​ቢ​ተ​ኛም ከተ​ዋ​ረ​ደው ሰው በማ​ይ​ከ​ብ​ር​በት ጊዜ፥ ታላ​ቁም ከታ​ናሹ በማ​ይ​ከ​ብ​ር​በት ጊዜ፥ የፍ​ርድ ቀን ናትና፥ የፍ​ዳና የቅ​ጣት ቀን ናትና፥ ሁሉም እንደ ሠራው የሚ​ቀ​በ​ል​ባት ቀን ናትና።

10 በጎ ሥራ የሠ​ሩም ዋጋ​ቸ​ውን የሚ​ቀ​በ​ሉ​ባት ቀን ናትና፥ ክፉ የሠ​ሩም ክፉ​ውን የሚ​ቀ​በ​ሉ​ባት ቀን ናትና።

11 ዋጋ​ቸ​ውን ያገ​ኙም ደስ የሚ​ሰ​ኙ​ባት ቀን ናትና፥ ክፉ​ው​ንም የተ​ቀ​በሉ የሚ​ያ​ዝ​ኑ​ባት ቀን ናትና። ሙታን አይ​ነ​ሡም እያሉ መጻ​ሕ​ፍ​ትን የሚ​ያ​ሳ​ብ​ሉ​ትም ያያሉ።

12 ያን​ጊ​ዜም የም​ድር ኃጥ​ኣን ስለ ሠሩት ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውና በም​ድር ሳሉ መል​ካም ባለ​ማ​ድ​ረ​ጋ​ቸው ስለ​ሚ​ያ​ገ​ኛ​ቸው መረ​ጋ​ጋት ስለ​ሌ​ለው ኀዘ​ና​ቸው ያለ​ቅ​ሳሉ።

13 እን​ደ​ዚ​ሁም በም​ድር ላይ ሳሉ በጎ ሥራን ሠር​ተ​ዋ​ልና በጎ ሥራን የሠሩ የደ​ጋ​ጎች ደስታ እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ አይ​ፈ​ጸ​ምም።

14 ከሞ​ትም እን​ደ​ሚ​ነሡ አው​ቀ​ዋ​ልና ከፈ​ጣ​ሪ​ያ​ቸው ሕግ አል​ወ​ጡም።

15 ከት​እ​ዛ​ዙም ስላ​ል​ወጡ ሁለት ሕይ​ወ​ትን ይወ​ር​ሳሉ፤ በም​ድ​ርም ላይ ዘራ​ቸ​ውን አበዛ፤ ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንም ባረ​ካ​ቸው።

16 በሰ​ማ​ያ​ትም በት​ን​ሣኤ ቀን ባለ​ጸ​ጎች በሚ​ደ​ኸ​ዩ​በት ጊዜ ለአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው የማ​ለ​ላ​ቸ​ውን መን​ግ​ሥተ ሰማ​ያ​ትን ያወ​ር​ሳ​ቸ​ዋል።

17 ክፉ የሚ​ሠ​ሩና የሙ​ታ​ንን መነ​ሣት የማ​ያ​ምኑ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሕግና የት​ን​ሣ​ኤ​ንም ቀን የማ​ያ​ስቡ ያለ​ቅ​ሳሉ።

18 ያን​ጊ​ዜም መጨ​ረሻ የሌ​ላት፥ ድኅ​ነ​ትና መረ​ጋ​ጋት የሌ​ለ​ባት የም​ታ​ገ​ኛ​ቸ​ውን መከራ ያያሉ፤ በል​ቡ​ና​ቸ​ውም መረ​ጋ​ጋ​ትና ዕረ​ፍት የሌ​ለው ኀዘን ይሆ​ናል።

19 የማ​ያ​ን​ቀ​ላፋ ትል፥ የማ​ይ​ጠ​ፋም እሳት ያገ​ኛ​ቸ​ዋል።

20 ሥጋ​ቸ​ውም ባለ​በት ቦታ እሳ​ትና ድኝ፥ ጥቅል ነፋስ፥ ውር​ጭና በረድ፥ ቀቅም በላ​ያ​ቸው ይዘ​ን​ማል።

21 የሙ​ታ​ን​ንም መነ​ሣት በማ​ያ​ምኑ ሰዎች ላይ ገሃ​ነመ እሳት አለ​ባ​ቸው።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች