Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 14 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 የአ​ይ​ሁ​ድና የሳ​ም​ራ​ው​ያን፥ የፈ​ሪ​ሳ​ው​ያ​ንና የሙ​ታ​ንን ትን​ሣኤ የማ​ያ​ምኑ የሰ​ዱ​ቃ​ው​ያን ነገር እኔን እጅግ ያሳ​ዝ​ነ​ኛል፤ ልቡ​ና​ዬም ያው​ቀ​ዋል። አይ​ሁድ፦ እን​ብላ፤ እን​ጠ​ጣም፤ ነገም እን​ሞ​ታ​ለን፤ በዚ​ያም የም​ና​የው የለም ይላሉ።

2 ሳም​ራ​ው​ያን ግን ሥጋ​ችን ትቢያ ይሆ​ና​ልና አይ​ነ​ሣም ይላሉ።

3 ትን​ሣ​ኤም በተ​ደ​ረገ ጊዜ የነ​ፍ​ሳ​ች​ንን መነ​ሣት እና​ም​ና​ለን። ነፍስ እንደ ነፋስ የማ​ት​ታ​ይና እንደ ነጐ​ድ​ጓድ ድምፅ ስለ ሆነች እነሆ እዚህ አለች የማ​ይ​ሏ​ትና የማ​ት​ታይ ስለ ሆነች ሥጋ ቢሞት አት​ሞ​ት​ምና።

4 ሥጋ​ችን ግን በሁሉ ትታ​ያ​ለች፤ ዐመ​ድና ትቢ​ያም ትሆ​ና​ለች። አው​ሬ​ዎች ይበ​ሏ​ታ​ልና፥ ትሎ​ችም በመ​ቃ​ብር ይበ​ሏ​ታ​ልና።

5 እነ​ዚ​ያም የበ​ሏት እንደ ሣር ይሆ​ና​ሉና፥ እን​ዳ​ል​ተ​ፈ​ጠ​ሩም ትቢያ ይሆ​ና​ሉና ዐመድ ይሆ​ናሉ፤ ፍለ​ጋ​ቸ​ውም አይ​ገ​ኝም። የፈ​ረሱ ሥጋ​ዎች የት ይገ​ኛሉ?

6 ፈሪ​ሳ​ው​ያ​ንም እን​ዲህ ይላሉ፥ “የሙ​ታ​ንን መነ​ሣት እና​ም​ና​ለን፤ ነገር ግን ነፍ​ሳ​ትን በም​ድር ያይ​ደለ በሰ​ማ​ያት ሌላ ሥጋ ያለ​ብ​ሳ​ቸ​ዋል።”

7 ሰዱ​ቃ​ው​ያ​ንም እን​ዲህ ይላሉ፥ “ነፍ​ሳ​ችን ከሥ​ጋ​ችን ከወ​ጣች በኋላ ከሞት አን​ነ​ሣም፤ ለነ​ፍ​ስና ለሥ​ጋም ትን​ሣኤ የላ​ቸ​ውም፤ ከሞ​ት​ንም በኋላ አን​ነ​ሣም።”

8 ስለ​ዚ​ህም እጅግ ፈጽ​መው ይስ​ታሉ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርና በጌ​ት​ነ​ቱም ላይ ጽር​ፈ​ትን ይና​ገ​ራ​ሉና የእ​ነ​ርሱ ነገር ያሳ​ዝ​ነ​ኛል።

9 የሚ​ያ​ጸ​ድ​ቃ​ቸው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም አላ​መ​ኑ​ት​ምና ለመ​ዳን ተስፋ የላ​ቸ​ውም፤ ለመ​ዳ​ንና ከሙ​ታን ለመ​ነ​ሣ​ትም ተስፋ የላ​ቸ​ውም።

10 አንተ ዕውር አይ​ሁ​ዳዊ ካለ​መ​ኖር የፈ​ጠ​ረ​ህን፥ እንደ ምራ​ቅም ስት​ሆን ሰው ያደ​ረ​ገ​ህን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አላ​ዋቂ ታደ​ር​ገ​ዋ​ለ​ህን? በም​ሳ​ሌ​ውና በመ​ልኩ የፈ​ጠ​ረህ ነፍ​ስ​ህ​ንና ሥጋ​ህን አዋ​ሕዶ ማስ​ነ​ሣት ይሳ​ነ​ዋ​ልን?

11 ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እጅ አታ​መ​ል​ጥ​ምና እን​ደ​ዚህ አታ​ስብ፤ ሳት​ወድ ትነ​ሣ​ለህ፤ በሞ​ት​ህም ጊዜ የተ​ያ​ዝ​ህ​ባት የሲ​ኦል ገመድ በአ​ን​ገ​ትህ አለ​ችና ሳት​ወድ ይፈ​ረ​ድ​ብ​ሃል።

12 በአ​ን​ገ​ትህ የታ​ሠ​ረች ያች ገመ​ድም በእ​ና​ትህ ማኅ​ፀን ከሲ​ኦል ግንድ ለአ​ንተ ትበ​ቅ​ላ​ለ​ችና። አን​ተም ባደ​ግህ ጊዜ እር​ሷም ታድ​ጋ​ለ​ችና።

13 አን​ተም በሞ​ትህ ጊዜ በአ​ን​ገ​ትህ ያኖ​ሯ​ታል፤ ግን​ዷ​ንም በሳ​ቧት ጊዜ እር​ስዋ ታመ​ጣ​ቸ​ዋ​ለች፤ ቅር​ን​ጫ​ፎ​ች​ዋ​ንም ትስ​ባ​ለች።

14 ኃጥ​ኣን ሁሉ በአ​ን​ገ​ታ​ቸው ገመድ እን​ዳለ በው​ስጧ ተይ​ዘው አሉና።

15 የኃ​ጥ​ኣ​ንም ነፍ​ሳት ሁሉ ከአ​ሉ​በት ከሰ​ማይ ዳርቻ ይመ​ጣሉ፤ እን​ደ​ዚ​ሁም ገመ​ድህ ነፍ​ስ​ህን ካለ​ህ​በት ስባ አም​ጥታ ወደ ሲኦል ታገ​ባ​ሃ​ለች።

16 ሥጋ​ህም ከነ​ፍ​ስህ ከተ​ለየ በኋላ እንደ አባ​ታ​ችን እንደ አዳም ሥጋ ፍጹም ሆኖ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በቸ​ር​ነቱ ጠል ይነ​ሣል። በዚ​ያም በደ​ል​ንና ኀጢ​አ​ትን እንደ ሠራህ እንደ አለ​ማ​መ​ንህ ፍዳ​ህን ትቀ​በ​ላ​ለህ።

17 ሌላ​ውን ብቻ የም​ታ​ስት አይ​ም​ሰ​ልህ፤ ራስ​ህም ትስ​ታ​ለህ፥ በስ​ሕ​ተ​ት​ህም በመ​ቃ​ብር ትኖ​ራ​ለህ፤ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ትእ​ዛዝ ወጥ​ተው ይስቱ ዘንድ የሙ​ታን ትን​ሣኤ የለም ትላ​ለህ።

18 እንደ ሠራ​ኸው ሥራህ ፍዳ​ህን ይሰ​ጥህ ዘንድ ያስ​ነ​ሣ​ሃል እንጂ በት​ቢ​ያና በዐ​መድ ውስጥ ማን ይተ​ው​ሃል?

19 ያን​ጊዜ ግን በነ​ፋስ ውስጥ ያለ ነፋስ ባሕ​ር​ይ​ህም ቢሆን፥ በውኃ ውስጥ ያለ ውኃ ባሕ​ር​ይ​ህም ቢሆን፤ በመ​ሬት ያለ መሬት ባሕ​ር​ይ​ህም ቢሆን፥ በእ​ሳ​ትም ውስጥ ያለ እሳት ባሕ​ር​ይ​ህም ቢሆን ይመ​ጣል።

20 በአ​ንተ ያደ​ረች፥ በጨ​ለማ ቦታ የም​ት​ኖር ነፍ​ስም ብት​ሆን ትመ​ጣ​ለች።

21 በገ​ነት በደ​ስታ የሚ​ኖሩ የጻ​ድ​ቃን ነፍ​ሳ​ትም ይመ​ጣሉ።

22 አን​ተም አይ​ሁ​ዳዊ፥ አን​ተም ሳም​ራዊ፥ አን​ተም ፈሪ​ሳዊ፥ አን​ተም ሰዱ​ቃዊ እስ​ኪ​ፈ​ረ​ድ​ብህ ድረስ በጨ​ለማ ትኖ​ራ​ለህ።

23 ያን​ጊ​ዜም ሰውን ስለ አሳ​ትህ እንደ ሥራህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ደ​ሚ​ከ​ፍ​ልህ ታያ​ለህ።

24 እን​ዲ​ህም ትላ​ቸ​ዋ​ለህ፦ የሞቱ ሰዎች አይ​ነ​ሡም፤ ነገ እን​ሞ​ታ​ለ​ንና እን​ብላ፤ እን​ጠ​ጣም፤ በሙ​ሴም ወን​በር ተቀ​ም​ጠህ በቃ​ልህ የሙ​ታን ትን​ሣኤ የለም ትላ​ለህ።

25 ስለ​ዚ​ህም የኦ​ሪ​ትን መጽ​ሐፍ እያ​ወ​ቅህ፥ የመ​ጻ​ሕ​ፍ​ት​ንም ቃል እያ​ስ​ተ​ማ​ርህ ሳትህ፤ ሰውን ከም​ታ​ስት ሳት​ማር በቀ​ረህ ይሻል ነበር።

26 በክፉ ትም​ህ​ር​ት​ህና በማ​ይ​ጠ​ቅም ቃልህ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሕዝብ ከም​ታ​ስ​ክድ የመ​ጻ​ሕ​ፍ​ትን ቃል በአ​ላ​ወ​ቅህ ይሻ​ልህ ነበር።

27 አንተ ግን እንደ ሥራ​ህና እንደ ከን​ፈ​ርህ ፍሬ ይሰ​ጥ​ሃል፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት አይቶ አያ​ዳ​ላ​ምና፥ በጎ ሥራ​ንም ለሚ​ያ​ስ​ተ​ምሩ ለወ​ዳ​ጆቹ ከአ​ዘ​ጋ​ጀው ጸጋ ይሰ​ጣ​ቸ​ዋ​ልና።

28 አን​ተም ከሚ​ፈ​ረ​ድ​ብህ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እጅ የም​ታ​መ​ል​ጥ​በት የለም፤ እንደ ሥራ​ህም ይከ​ፍ​ልህ ዘንድ አለው፤ አን​ተና ያስ​ተ​ማ​ር​ሃ​ቸ​ውም በአ​ን​ድ​ነት ይፈ​ረ​ድ​ባ​ች​ኋል።

29 ሙታን እን​ደ​ሚ​ነ​ሡም ዕወቅ፤ ሕጉን የጠ​በቁ ቢሆ​ኑም ይነ​ሣሉ፤ በመ​ቃ​ብር መቈ​የት አይ​ች​ሉም፤ ዝናም በዘ​ነመ ጊዜ ምድር ሣርን እን​ደ​ም​ታ​ወጣ ትእ​ዛዙ ያወ​ጣ​ቸ​ዋ​ልና።

30 ዝናም ምድ​ርን ባጠ​ገ​ባት ጊዜ ርጥብ እን​ጨት ቅጠ​ልን እን​ደ​ም​ታ​ወጣ፥ ስን​ዴም ፍሬን እን​ደ​ም​ታ​ፈራ፥ እህ​ልም ዝር​ዝ​ርን እን​ደ​ም​ታ​ስ​ገኝ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከወ​ደደ ፍሬ​ዋን ትከ​ለ​ክል ዘንድ እን​ደ​ማ​ት​ችል፥

31 የፀ​ነ​ሰ​ችም ሴት ምጥ በያ​ዛት ጊዜ ማኅ​ፀ​ኗን መዝ​ጋት፥ ሳት​ወ​ል​ድም ማም​ለጥ እን​ደ​ማ​ት​ችል።

32 ምድ​ርም እን​ደ​ዚሁ በእ​ር​ስዋ የተ​ሰ​በ​ሰ​ቡ​ትን ታወ​ጣ​ለች፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ቃል ከሰ​ማች በኋላ ማኅ​ፀ​ን​ዋን መዝ​ጋት አት​ች​ልም፥ ነገር ግን ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የታ​ዘዘ ጠል ወደ እር​ስዋ ይወ​ር​ዳ​ልና በአ​ንድ ጊዜ ትወ​ል​ዳ​ቸ​ዋ​ለች።

33 ሥጋ​ዎ​ችም ሬሳ​ዎ​ቻ​ቸው በወ​ደ​ቁ​ባ​ቸው ቦታ​ዎች ይሰ​በ​ሰ​ባሉ፤ የነ​ፍ​ሳት መዛ​ግ​ብት ቤቶ​ችም ይከ​ፈ​ታሉ፤ ነፍ​ሳ​ትም ቀድሞ ወደ ተለ​ዩ​በት ወደ ሥጋ ይመ​ለ​ሳሉ።

34 መለ​ከ​ትም በተ​ነፋ ጊዜ ሙታን እንደ ዐይን ጥቅሻ ይነ​ሣሉ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት ይቆ​ማሉ፥ እንደ እጃ​ቸ​ውም ሥራ ይሰ​ጣ​ቸ​ዋል።

35 ያን​ጊ​ዜም ከሙ​ታን ጋራ እን​ደ​ም​ት​ነሣ ታያ​ለህ፤ በም​ድር ላይ የሠ​ራ​ኸ​ው​ንም ሥራ ሁሉ ታደ​ን​ቃ​ለህ፤ በዐ​ይ​ኖ​ች​ህም ፊት ተጽ​ፈው ባየ​ሃ​ቸው ጊዜ ያን​ጊዜ የማ​ይ​ረባ ጸጸ​ትን ትጸ​ጸ​ታ​ለህ።

36 ከሙ​ታን ጋራም እን​ደ​ም​ት​ነሣ፥ እንደ ሠራ​ኸ​ውም ሥራ እን​ደ​ም​ት​ቀ​በል ታው​ቃ​ለህ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች