Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 13 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 የአ​መኑ እሊያ አም​ስቱ የመ​ቃ​ቢስ ልጆች ግን ለጣ​ዖት የተ​ሠ​ዋ​ውን መሥ​ዋ​ዕት መብ​ላ​ትን እንቢ ብለው ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውን ለሞት ሰጡ።

2 ይህ ዓለም እን​ደ​ሚ​ያ​ረ​ጅና እን​ደ​ሚ​ያ​ልፍ፥ ተድ​ላ​ውም ለዘ​ለ​ዓ​ለም እን​ደ​ማ​ይ​ኖር ዐው​ቀው በሰ​ማይ ከአ​ለው እሳት ይድኑ ዘንድ ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውን ለእ​ሳት ሰጡ።

3 ሰውን ከመ​ገ​ዳ​ደር እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መገ​ዳ​ደር እን​ደ​ሚ​ከፋ፥ ከን​ጉ​ሥም ቍጣ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቍጣ እን​ደ​ሚ​ከፋ አው​ቀ​ዋ​ልና።

4 “አቤቱ፥ በም​ድር ላይ ብዙ ዘመን ከመ​ኖር በገ​ነት አን​ዲት ቀን ደስ መሰ​ኘት ይሻ​ላል፤ ከብዙ ዘመ​ኖ​ችም የአ​ን​ዲት ሰዓት ይቅ​ር​ታህ ይሻ​ላል፤

5 የእኛ የሰ​ዎች ዘመ​ና​ችን ምን​ድን ነው? እንደ ጥላ የሚ​ያ​ልፍ፥ በእ​ሳት ዳርም እንደ አለ ሰም አይ​ደ​ለ​ምን?

6 አቤቱ አንተ ግን ለዘ​ለ​ዓ​ለም ትኖ​ራ​ለህ፤ ዘመ​ን​ህም የማ​ይ​ፈ​ጸም ነው፤ ስም አጠ​ራ​ር​ህም ለልጅ ልጅ ነው።”

7 የመ​ቃ​ቢስ ልጆ​ችም ይኸ​ንና የሚ​መ​ስ​ለ​ውን ሁሉ ዘመሩ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መታ​መ​ንን መረጡ፤ ርኩስ መሥ​ዋ​ዕ​ትን መብ​ላ​ት​ንም እንቢ አሉ፤

8 ስለ​ዚ​ህም ሙታን እን​ደ​ሚ​ነሡ፥ ከት​ን​ሣ​ኤም በኋላ ፍርድ እን​ደ​ሚ​ፈ​ረድ ዐው​ቀው ስለ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ብለው ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውን ለሰ​ማ​ዕ​ት​ነት ሰጡ።

9 የሙ​ታ​ንን ትን​ሣኤ የማ​ታ​ው​ቁና የማ​ታ​ምኑ ሰዎች! ከዚች ከም​ታ​ልፍ ከም​ድ​ራ​ዊት ሕይ​ወ​ታ​ቸው ይልቅ ኋለ​ኛ​ዪቱ ሕይ​ወ​ታ​ቸው እን​ደ​ም​ት​በ​ልጥ ዐው​ቀው ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውን በአ​ን​ድ​ነት ለሞት ከሰ​ጡና ወን​ድ​ማ​ማ​ች​ነ​ታ​ቸው ከአ​ማረ ከእ​ነ​ዚህ ከአ​ም​ስቱ ሰዎች የተ​ነሣ ዕወቁ፤

10 ሁሉ እን​ዲ​ያ​ልፍ ዐው​ቀው ስላ​መ​ኑ​በት፥ ለጣ​ዖ​ትም ስላ​ል​ሰ​ገዱ፥ የሞ​ተ​ው​ንና የረ​ከ​ሰ​ው​ንም መሥ​ዋ​ዕት ስላ​ል​በሉ፥ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምስ​ጋ​ናን ያገኙ ዘንድ ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውን ለሞት ሰጡ።

11 ስለ​ዚ​ህም በኋ​ለ​ኛ​ዪቱ ቀን በነ​ፍ​ስና በሥጋ ደስ እን​ደ​ሚ​ያ​ሰ​ኛ​ቸው ዐው​ቀው ሚስ​ትና ልጆች እያ​ሏ​ቸው የዚ​ህን ዓለም ጣዕ​ምና የሞ​ትን ምሬት አላ​ወ​ቁም፤ በኋ​ለ​ኛ​ዪ​ቱም ቀን በነ​ፍ​ስና በሥጋ ትን​ሣኤ እን​ዲ​ደ​ረግ ዐው​ቀው ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውን ለሞት ሰጡ።

12 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሥር​ዐት የጠ​በቁ ሕማ​ምና ኀዘን፥ ሞትም በሌ​ለ​በት በሚ​መ​ጣው ዓለም ለልጅ ልጅና ለረ​ጅም ዘመን፥

13 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ከአ​መኑ ደጋግ ነገ​ሥ​ታ​ትና መኳ​ን​ንት ጋር እን​ደ​ሚ​ነ​ግሡ ዐው​ቀው፥ ኋላም የሚ​ደ​ረ​ገ​ውን በል​ቡ​ና​ቸው አይ​ተው፥ በእ​ሳት መካ​ከል እንደ ሰም ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውን ለሞት ሰጡ።

14 ፊታ​ቸ​ውም ከፀ​ሐይ ሰባት እጅ እን​ደ​ሚ​ያ​በራ፥ ሁሉም በነ​ፍ​ስና በሥጋ በሚ​ነሣ ጊዜ በፍ​ቅሩ ደስ እን​ደ​ሚ​ላ​ቸው ተስፋ አድ​ር​ገው ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውን ለሞት ሰጡ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች