Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 11 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሰው ሙሴን አስ​በው፤ በጸ​ሎ​ቱና በት​ሕ​ት​ናው ይህን ያህል ሕዝ​ቡን ሲጠ​ብቅ አል​ተ​በ​ሳ​ጨም፥ አላ​ጠ​ፋ​ምም፤ ነገር ግን ላሙ​ትና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በአ​ንድ ጊዜ ያጠ​ፋ​ቸው ዘንድ ለወ​ደደ ለወ​ን​ድ​ሙና ለእ​ኅቱ በየ​ዋ​ህ​ነቱ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውን እን​ዲህ ሲል አስ​ተ​ሰ​ረ​የ​ላ​ቸው፥ “አቤቱ ወገ​ኖ​ችህ በፊ​ትህ በድ​ለ​ዋ​ልና ወገ​ኖ​ች​ህን ይቅር በል፤ ቸልም አት​በል፥

2 በፊ​ትህ በድ​ያ​ለ​ሁና ኀጢ​አ​ተኛ የም​ሆን እኔን ባር​ያ​ህን ይቅር በለኝ፤ አንተ መሓሪ ነህና፥ ይቅር ባይም ነህና ለእ​ነ​ር​ሱም አስ​ተ​ስ​ር​ይ​ላ​ቸው።”

3 እን​ደ​ዚ​ህም ሙሴ ለአ​ሙት አስ​ተ​ሰ​ረ​የ​ላ​ቸው።

4 ስለ​ዚ​ህም የዋህ ተባለ።

5 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከወ​ን​ድ​ሞቹ ከሌ​ዋ​ው​ያኑ ልጆች ሁሉ ይልቅ እጅግ ወደ​ደው፤ ካህ​ና​ቱ​ንም ይሾ​ማ​ቸ​ዋ​ልና በእ​ነ​ርሱ ዘንድ እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አስ​መ​ሰ​ለው።

6 የተ​ደ​ፋ​ፈሩ የቆ​ሬን ልጆች ግን በም​ድር በታች አሰ​ጠ​ማ​ቸው፤ በሥ​ጋና በነ​ፍስ ሕያ​ዋን ሳሉ ከከ​ብ​ቶ​ቻ​ቸ​ውና ከድ​ን​ኳ​ኖ​ቻ​ቸው ጋራ ወደ ሲኦል አወ​ረ​ዳ​ቸው፤ ፈጣ​ሪው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ወድ​ዶ​ታ​ልና ከት​እ​ዛ​ዙም አል​ወ​ጣ​ምና የተ​ና​ገ​ረው ቃል ሁሉ እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ይደ​ረ​ግ​ለት ነበር።

7 አን​ተም እን​ዲሁ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ትእ​ዛዝ ባት​ተ​ላ​ለፍ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፈቃ​ድ​ህን ያደ​ር​ግ​ል​ሃል፤ ነገ​ር​ህ​ንም ይወ​ድ​ል​ሃል፤ መን​ግ​ሥ​ት​ህ​ንም ይጠ​ብ​ቅ​ል​ሃል።

8 ከሙሴ ትእ​ዛዝ የወጡ የቆ​ሬና የአ​ሳፍ ልጆ​ችም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ልቡ​ና​ች​ሁን አቅኑ ስላ​ላ​ቸው በእ​ርሱ አን​ጐ​ራ​ጐሩ።

9 “እኛስ በም​ስ​ክሩ ድን​ኳን የክ​ህ​ነት ሥራ የም​ን​ሠራ የሌዊ ልጆች አይ​ደ​ለ​ን​ምን?” አሉት።

10 ያጥ​ኑም ዘንድ ጥና​ቸ​ውን ያዙ፤ ሄደ​ውም አጠኑ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን ጸሎ​ታ​ቸ​ውን አል​ተ​ቀ​በ​ለም፤ በጥ​ና​ቸው እሳ​ትም ተቃ​ጠሉ፤ በእ​ሳት እን​ደ​ሚ​ቀ​ልጥ ሰምም ቀለጡ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም አንድ ሰው ስንኳ አል​ቀ​ረም፤ “በሰ​ው​ነ​ታ​ቸው መቃ​ጠል ጥና​ቸው ከብ​ሯል” ብሏ​ልና በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትእ​ዛዝ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ማደ​ሪያ ከገ​ቡት ከጥ​ና​ቸው በቀር ልብ​ሶ​ቻ​ቸ​ውና አጥ​ን​ቶ​ቻ​ቸው አል​ቀ​ሩም።

11 ስለ​ዚ​ህም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሙሴ​ንና አሮ​ንን እን​ዲህ አላ​ቸው፥ “ጥና​ቸ​ውን ወደ ድን​ኳን ሰብ​ስቡ፤ ከውጭ ጀምሮ እስከ ውስጥ ድረስ ሁሉን ላዘ​ጋ​ጀ​ሁ​ለት ለቤቴ መሣ​ሪያ ይሁን።”

12 የተ​ቀ​ደ​ሰች የድ​ን​ኳ​ን​ዋ​ንም መሣ​ሪያ አዘ​ጋጀ፤ መክ​ደ​ኛ​ው​ንና ቀለ​በ​ቱን፥ የኪ​ሩ​ቤ​ልን ሥዕ​ልና ባሕ​ሩን አዘ​ጋጀ።

13 ሰኑ​ንና መጋ​ረ​ጃ​ውን፥ ስክ​ተ​ቱ​ንና የድ​ን​ኳ​ኑን ዙሪያ ዕድሞ፥ ጋኖ​ች​ንና በም​ስ​ክሩ ድን​ኳን የሚ​ሠ​ዉ​በት መሠ​ዊ​ያ​ውን ሠራ።

14 የፈ​ቃ​ዱን መሥ​ዋ​ዕ​ትና የሰ​ላ​ሙን መሥ​ዋ​ዕት፥ የስ​እ​ለ​ቱ​ንና የኀ​ጢ​አ​ቱን መሥ​ዋ​ዕት፥ የማ​ታ​ው​ንና የጧ​ቱ​ንም መሥ​ዋ​ዕት ሠዉ።

15 ሥራ ይሠ​ሩ​ባት ዘንድ በም​ስ​ክሩ ድን​ኳን ለሙሴ ያዘ​ዘ​ውን ሁሉ አዘ​ዛ​ቸው።

16 ማርና ወተ​ትን የም​ታ​ስ​ገኝ፥ ለአ​ብ​ር​ሃም የማ​ለ​ለ​ትን፥ ያባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ርስት ይሰ​ጣ​ቸው ዘንድ ተስፋ በሰ​ጣ​ቸው በፈ​ጣ​ሪ​ያ​ቸው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሕጉ ድን​ኳን ውስጥ ስሙ በእ​ነ​ርሱ ይመ​ሰ​ገን ዘንድ ለአ​ም​ላ​ካ​ቸው መገ​ዛ​ትን አላ​ቃ​ለ​ሉም።

17 ለይ​ስ​ሐቅ ማለ​ለት፤ ለያ​ዕ​ቆ​ብም አም​ል​ኮ​ቱን አጸ​ና​ለት።

18 በም​ስ​ክሩ ድን​ኳ​ንም ለሙ​ሴና ለአ​ሮን አጸ​ና​ላ​ቸው፥

19 በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም በድ​ን​ኳ​ኑና ሰሎ​ሞን በሠ​ራው ቤተ መቅ​ደስ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ማደ​ሪያ፥ የል​ዑ​ልም የስሙ ማረ​ፊያ፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ቅዱስ ማደ​ሪያ እስ​ኪ​ሆን ድረስ ለሳ​ሙ​ኤ​ልና ለኤ​ል​ያስ አም​ል​ኮ​ቱን አጸ​ና​ላ​ቸው።

20 በየ​ዋ​ህ​ነት ለሚ​ኖሩ ለካ​ህ​ናቱ የሚ​ገ​ለ​ጥ​ባት መለ​መ​ኛና የኀ​ጢ​አት ማስ​ተ​ስ​ረያ ናትና።

21 ፈቃ​ዱ​ንም ለሚ​ያ​ደ​ርጉ ሰዎች ልመ​ና​ቸ​ውን የሚ​ሰ​ማ​ባት ቦታ ናት።

22 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ቅዱስ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕጉ የሚ​ሠ​ራ​ባት ናትና።

23 ለእ​ስ​ራ​ኤል ቅዱስ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በጎ መዓዛ ሊሆን መሥ​ዋ​ዕት የሚ​ሠ​ዋ​ባት፥ ዕጣ​ንም የሚ​ታ​ጠ​ን​ባት ናትና።

24 በም​ስ​ክሩ ድን​ኳን ውስ​ጥም ይቅር በሚ​ል​በት በመ​ክ​ደ​ኛው ላይ ሆኖ ይና​ገር ነበር፤ ለመ​ረ​ጣ​ቸው ለያ​ዕ​ቆብ ልጆች፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሕ​ጉና በት​እ​ዛዙ ጸን​ተው ለሚ​ኖሩ ለቅ​ዱ​ሳ​ኑም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ብር​ሃኑ ይገ​ለ​ጥ​ላ​ቸው ነበር።

25 የሚ​ገ​ዳ​ደሩ ግን ምድር እን​ዳ​ሰ​ጠ​መ​ቻ​ቸው እንደ ቆሬ ልጆች ይሆ​ናሉ፤ እን​ዲ​ሁም ኃጥ​ኣን እስከ ዘለ​ዓ​ለም ድረስ መውጫ ወደ​ሌ​ላት ወደ ገሃ​ነም እሳት ይገቡ ዘንድ አላ​ቸው።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች