Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 10 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 እና​ን​ተም ነገ​ሥ​ታ​ቱና መኳ​ን​ንቱ በሰ​ይ​ጣን ጎዳና አት​ሂዱ። ነገር ግን የፈ​ጠ​ራ​ች​ሁን፥ እስከ ዛሬም ድረስ የጠ​በ​ቃ​ች​ሁን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፍሩት።

2 ሁሉ​ንም በሚ​ገዛ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግና ትእ​ዛዝ ጸን​ታ​ችሁ ኑሩ።

3 የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች የኬ​ጤ​ዎ​ን​ንና የከ​ና​ኔ​ዎ​ንን፥ የፌ​ር​ዜ​ዎ​ን​ንም ሀገር ይወ​ርሱ ዘንድ ወደ አማ​ሌቅ በመጡ ጊዜ የሴ​ፎር ልጅ ባላቅ፥

4 በለ​ዓ​ምን፥ “አንተ የረ​ገ​ም​ኸው የተ​ረ​ገመ፥ የመ​ረ​ቅ​ኸ​ውም የተ​መ​ረቀ ነውና ትረ​ግ​ም​ልኝ ዘንድ ና፤ እኔም የሚ​ያ​ከ​ብ​ር​ህን ብዙ ወር​ቅና ብር እሰ​ጥ​ሃ​ለሁ” ብሎ​ታ​ልና።

5 በለ​ዓ​ምም የጥ​ን​ቆ​ላ​ውን ዋጋ ተስፋ አድ​ርጎ መጣ፤ የሴ​ፎር ልጅ ባላ​ቅም የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች የሰ​ፈ​ሩ​በ​ትን ቦታ አሳ​የው፤

6 ሟር​ቱ​ንም አደ​ረገ፤ መሥ​ዋ​ዕ​ቱ​ንም ሠዋ፤ የሰ​ቡ​ት​ንም ላሞ​ች​ንና በጎ​ችን አረደ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ልጆች ይረ​ግ​ማ​ቸው ዘንድ ወደደ።

7 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን ይረ​ግ​ማ​ቸው ዘንድ አል​ወ​ደ​ደም፤ ርግ​ማ​ንን ወደ ምር​ቃት በቃሉ መለ​ሳት እንጂ።

8 እን​ዲ​ህም አለ፥ “አንተ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የመ​ረ​ጠው ሕዝብ ነህና፥ ከሰ​ማይ የሚ​መጣ የፍ​ቁር ማደ​ሪ​ያም ነህና የሚ​መ​ር​ቁህ የተ​መ​ረቁ ይሁኑ፤ የሚ​ረ​ግ​ሙ​ህም የተ​ረ​ገሙ ይሁኑ” አለ።

9 ከዚ​ህም በኋላ በፊቱ በመ​ረ​ቃ​ቸው ጊዜ የሴ​ፎር ልጅ ባላቅ አዘነ፤ ፈጽ​ሞም ተቈጣ፤ ይረ​ግ​ማ​ቸ​ውም ዘንድ አዘዘ።

10 በለ​ዓ​ምም፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የመ​ረ​ቀው ወገን ወደ​ዚህ ሀገር መጥ​ት​ዋ​ልና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የመ​ረ​ቃ​ቸ​ውን እኔ አል​ረ​ግ​ምም” አለው።

11 የሴ​ፎር ልጅ ባላ​ቅም በለ​ዓ​ምን አለው፥ “እኔ ትረ​ግ​ም​ልኝ ዘንድ ወድጄ ነበር፤ አንተ ግን አል​ረ​ገ​ም​ኻ​ቸ​ውም፤ በፊ​ቴም ፈጽ​መህ መረ​ቅ​ኻ​ቸው፤ አን​ተም ብት​ረ​ግ​ም​ል​ኝና ስጠኝ ብት​ለኝ እኔ ቤት ሙሉ ወር​ቅና ብር በሰ​ጠ​ሁህ ነበር፤ አንተ ግን ፈጽ​መህ መረ​ቅ​ኻ​ቸው፤ ለእ​ኔም በጎ አላ​ደ​ረ​ግ​ህም፤ እኔም ለአ​ንተ በጎ ነገር አላ​ደ​ር​ግም።”

12 በለ​ዓ​ምም፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በአ​ን​ደ​በቴ ያደ​ረ​ገ​ውን ቃል እር​ሱን እና​ገ​ራ​ለሁ እንጂ እኔስ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ቸል ማለ​ትና መተ​ላ​ለፍ አል​ች​ልም።

13 እኔስ ከነ​ፍሴ ገን​ዘ​ብን አል​ወ​ድ​ድም፤ ገን​ዘ​ብን ብወድ የተ​መ​ረቀ ወገ​ንን እን​ዳ​ል​ረ​ግም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይቈ​ጣ​ኛ​ልና” አለ።

14 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አባ​ታ​ቸው ያዕ​ቆ​ብን፥ “የሚ​መ​ር​ቁህ የተ​መ​ረቁ ይሁኑ፤ የሚ​ረ​ግ​ሙ​ህም የተ​ረ​ገሙ ይሁኑ” ብሎ​ታ​ልና፤

15 የሚ​መ​ር​ቅ​ህም ሁሉ የተ​መ​ረቀ ነው፤ ያለ ፍር​ድም የሚ​ረ​ግ​ምህ የተ​ረ​ገመ ነው፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አን​ተን ይወ​ድህ ዘንድ ጎዳ​ና​ህ​ንና ሥራ​ህን አከ​ና​ውን።

16 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም በክ​ፋ​ታ​ቸው እን​ዳ​ሳ​ዘ​ኑት፥ እር​ሱም ቸል እን​ዳ​ላ​ቸው እንደ ቀደሙ ሰዎች አት​ሁን፤ በጥ​ፋት ውኃም ያጠ​ፋ​ቸው አሉ።

17 በጠ​ላ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም እጅ ያጠ​ፋ​ቸው አሉ፤ መከራ ያጸ​ኑ​ባ​ቸው ክፉ​ዎች ጠላ​ቶ​ችን አም​ጥቶ ነገ​ሥ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ከካ​ህ​ና​ቶ​ቻ​ቸ​ውና ከነ​ቢ​ያ​ቶ​ቻ​ቸው ጋራ ማረ​ኳ​ቸው።

18 ወደ​ማ​ያ​ው​ቁት ወደ ባዕድ ሀገ​ርም አደ​ረ​ሷ​ቸው፤ ፈጽ​መ​ውም ማረ​ኳ​ቸው፤ ገረ​ፉ​አ​ቸ​ውም፤ ሀገ​ራ​ቸ​ው​ንም አጠፉ።

19 የቅ​ድ​ስ​ቲ​ቱን ከተማ አጥ​ሯ​ንና ቅጥ​ሯን አፍ​ር​ሰ​ዋ​ልና ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምን እንደ እርሻ አደ​ረ​ጓት።

20 ካህ​ና​ቱም ተማ​ረኩ፤ ሕጉም ፈረሰ፤ አር​በ​ኞ​ችም በጦር ወደቁ።

21 ባል​ቴ​ቶ​ችም ተማ​ረኩ፤ ለሞቱ ባሎ​ቻ​ቸ​ውም አላ​ለ​ቀ​ሱም፤ ተማ​ር​ከ​ዋ​ልና ለራ​ሳ​ቸው አለ​ቀሱ፤

22 ሕፃ​ና​ትም አለ​ቀሱ፤ ሽማ​ግ​ሎ​ችም አፈሩ፤ የሽ​ማ​ግ​ሌ​ው​ንና የሽ​በ​ታ​ሙን ፊት አል​ራ​ሩም።

23 ለቆ​ን​ጆ​ዎ​ችና በሕግ ላሉም አል​ራ​ሩም፤ በአ​ገ​ራ​ቸው ያገ​ኙ​ት​ንም ሁሉ አጠፉ፤ ቤተ መቅ​ደ​ስን አስ​ቀ​ድሞ ያፈ​ርስ ዘንድ በወ​ደደ ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ወገ​ኖ​ቹን ተቈ​ጥ​ት​ዋ​ልና ወደ​ማ​ያ​ው​ቁት ወደ ባዕድ ሀገር ማር​ከው ወሰ​ዷ​ቸው።

24 ስለ​ዚ​ህም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች ቸል ባላ​ቸው ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምን እንደ እርሻ እን​ድ​ት​ታ​ረስ አደ​ረ​ጋት፤ ሁል​ጊዜ ፈጣ​ሪ​ያ​ቸ​ውን ያሳ​ዝ​ኑ​ታ​ልና።

25 እርሱ ግን በም​ንም አንድ ጊዜ አላ​ጠ​ፋ​ቸ​ውም፤ ስለ አባ​ቶ​ቻ​ቸው ይራ​ራ​ላ​ቸ​ዋ​ልና የሚ​ራ​ራ​ላ​ቸው ስለ ራሳ​ቸው አይ​ደ​ለም። በእ​ው​ነት የነ​ገሡ፥ በፈ​ጣ​ሪ​ያ​ቸ​ውም ፊት በቀና ሕግ ጸን​ተው የኖሩ አባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን አብ​ር​ሃ​ም​ንና ይስ​ሐ​ቅን ያዕ​ቆ​ብ​ንም ይወ​ዳ​ቸ​ዋ​ልና ነው እንጂ።

26 እር​ሱም እጥፍ በሆነ ክብር ላይ ሾማ​ቸው፤ በሰ​ማ​ይና በም​ድር ያለ ሁለት መን​ግ​ሥ​ት​ንም አገኙ።

27 እን​ዲ​ሁም በሚ​ያ​ልፍ በዚህ ዓለም የም​ት​ኖሩ እና​ንተ ነገ​ሥ​ታ​ቱና መኳ​ን​ንቱ በሚ​ገባ ሥራ ጸን​ተው የኖሩ ከእ​ና​ንተ አስ​ቀ​ድሞ የነ​በሩ አባ​ቶ​ቻ​ችሁ መን​ግ​ሥተ ሰማ​ያ​ትን እንደ ወረሱ፥ ስማ​ቸው ለልጅ ልጅ ያማረ እንደ ሆነ አስ​ቧ​ቸው።

28 አን​ተም መን​ግ​ሥ​ት​ህን ያቀ​ና​ልህ ዘንድ መል​ካም አኑ​ዋ​ኑ​ዋ​ራ​ቸው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እን​ዳ​ገ​ለ​ገ​ሉት ከአ​ንተ አስ​ቀ​ድሞ እንደ ነበሩ እንደ ደጋ​ጎች ነገ​ሥ​ታት ስም​ህን መል​ካም ያደ​ር​ግ​ልህ ዘንድ ሥራ​ህን አቅና።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች