Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ መቃ​ብ​ያን ካልእ 1 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 መቃ​ቢስ አይ​ሁ​ድን በሶ​ርያ በሁ​ለቱ ወን​ዞች መካ​ከል አግ​ኝቶ ከኢ​ያ​ቦቅ ጀምሮ እስከ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም አደ​ባ​ባይ ድረስ በሸ​ለ​ቆ​ዎ​ቻ​ቸው እንደ ገደ​ላ​ቸው፥ ቅድ​ስ​ቲ​ቱ​ንም ከተማ እን​ዳ​ጠ​ፋት የሚ​ና​ገር መጽ​ሐፍ ይህ ነው።

2 ከሰ​ማ​ርያ ጀምሮ እስከ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም አደ​ባ​ባይ ድረስ፥ እስከ አው​ራ​ጃ​ዋም ሁሉ ድረስ ሰፍ​ረ​ዋ​ልና ከጥ​ቂ​ቶች በቀር ሳያ​ስ​ቀሩ በጦር ገደሉ። ኤዶ​ማ​ው​ያ​ንና ሶር​ያ​ው​ያን፥ አማ​ሌ​ቃ​ው​ያ​ንም የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምን ከተማ ካጠ​ፋው ከሞ​ዓብ ሰው ከመ​ቃ​ቢስ ጋር አንድ ሆነ​ዋ​ልና።

3 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች በበ​ደሉ ጊዜ ሞዓ​ባ​ዊ​ውን መቃ​ቢ​ስን አስ​ነ​ሣ​ባ​ቸው፤ እር​ሱም ሁሉን በሰ​ይፍ ገደ​ላ​ቸው።

4 ስለ​ዚ​ህም ነገር የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጠላ​ቶች በቅ​ድ​ስት ከተ​ማው ላይ ደነፉ፤ በወ​ን​ጀ​ላ​ቸ​ውም ተማ​ማሉ።

5 ኤዶ​ማ​ው​ያ​ንና ኢሎ​ፍ​ላ​ው​ያ​ንም ሰፈሩ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ስለ ተገ​ዳ​ደሩ እርሱ ልኳ​ቸ​ዋ​ልና የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ከተማ ይበ​ቀሉ ጀመር።

6 የዚ​ያም የመ​ቃ​ቢስ ሀገሩ የሞ​ዓብ ሬማት ናት፤ ከሀ​ገ​ሩም በኀ​ይል ተነ​ሥቶ አብ​ረ​ውት ከአሉ ሰዎች ጋራ ተማ​ማለ።

7 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ከተማ ያጠፉ ዘንድ በመ​ስ​ጴ​ጦ​ምያ-ጌላ​ቡሄ ሸለ​ቆ​ዎች እስከ ሶርያ ድረስ ሰፈሩ፤ በዚ​ያም ኢሎ​ፍ​ላ​ው​ያ​ን​ንና አማ​ሌ​ቃ​ው​ያ​ንን ለመነ፤ በወ​ን​ጀ​ልም ከእ​ርሱ ጋራ አንድ ይሆኑ ዘንድ ብዙ ወር​ቅ​ንና ብርን፥ ፈረ​ሶ​ች​ንና ሠረ​ገ​ላ​ዎ​ችን ሰጣ​ቸው።

8 በአ​ን​ድ​ነ​ትም መጥ​ተው አን​ባ​ዪ​ቱን ናዷት፤ በው​ስጧ የሚ​ኖሩ ሰዎች ደም​ንም እንደ ውኃ አፈ​ሰሱ።

9 ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ም​ንም እንደ ተክል ጠባቂ ጎጆ አደ​ረ​ጓት፤ በው​ስ​ጧም ድምፅ አሰ​ማ​ባት፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የማ​ይ​ወ​ድ​ደ​ውን የክ​ፋት ሥራ ሁሉ አደ​ረገ፤ ጽድ​ቅ​ንና ቅድ​ስ​ናን የተ​መ​ላች የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ከተማ አረ​ከሱ።

10 “የባ​ሮ​ች​ህን እሬሳ ለሰ​ማይ ወፎች ምግብ አደ​ረጉ። የጻ​ድ​ቃ​ን​ህ​ንም ሥጋ ለም​ድረ በዳ አራ​ዊት መብል አደ​ረጉ።”

11 ባል​ቴ​ቲ​ቱ​ንና የሙት ልጁን ቀሙ፤ ሰይ​ጣን እን​ዳ​ስ​ተ​ማ​ራ​ቸው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ሳይ​ፈሩ አድ​ር​ገ​ዋ​ልና ኵላ​ሊ​ት​ንና ልቡ​ናን የሚ​መ​ረ​ምር እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እስ​ኪ​ቈጣ ድረስ በፀ​ነሱ ሴቶች ሆድ ያለ​ውን ፅንስ አወጡ።

12 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕዝ​ብም ላይ ክፉን ስለ አደ​ረጉ ደስ እያ​ላ​ቸው ወደ ሀገ​ራ​ቸው ተመ​ለሱ፤ ከቅ​ድ​ስት ከተማ የማ​ረ​ኩ​ት​ንም ምርኮ ወሰዱ።

13 ተመ​ል​ሰ​ውም ወደ ቤታ​ቸው በገቡ ጊዜ ደስ​ታን፥ ዘፈ​ን​ንና ጭብ​ጨ​ባን አደ​ረጉ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች