Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ዕዝራ ሱቱ​ኤል 10 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


በን​ስር አም​ሳል ያየው አም​ስ​ተ​ኛው ራእይ

1 ከዚ​ህም በኋላ በማ​ግ​ሥቱ ሌሊት ንስር ከባ​ሕር ሲወጣ በሕ​ልም አየሁ፤ ክን​ፎ​ቹም ዐሥራ ሁለት ናቸው፤ ራሶ​ቹም ሦስት ናቸው።

2 በክ​ን​ፎ​ቹም በዓ​ለሙ ሁሉ ይበ​ር​ራል፤ የሰ​ማይ ነፋ​ሳ​ትም ሁሉ ይነ​ፍ​ሱ​በ​ታል፤ ደመ​ና​ትም በእ​ርሱ ይሰ​በ​ሰ​ባሉ።

3 ከእ​ነ​ዚ​ያም ክን​ፎች ራሶች ይበ​ቅ​ላሉ፤ እነ​ዚ​ያም ራሶች ደቃ​ቅና ታና​ናሽ ክንፍ ይሆ​ናሉ፤

4 ራሶ​ቹም ዝም ይላሉ፤ ከእ​ነ​ዚ​ያም ራሶች መካ​ከ​ለ​ኛው ራስ ይበ​ል​ጣል፤ ነገር ግን እር​ሱም ከእ​ነ​ርሱ ጋር ዝም ይላል።

5 ያም ንስር ምድ​ር​ንና በም​ድር የሚ​ኖ​ሩ​ትን ይገዛ ዘንድ በክ​ን​ፎቹ ይበ​ር​ራል፤

6 ከሰ​ማይ በታች ያለ ሁሉ ይገ​ዛ​ለት ዘንድ ያን ንስር በም​ድር ከተ​ፈ​ጠ​ረው ፍጥ​ረት የሚ​ከ​ራ​ከ​ረው ማንም የለም።

7 ከዚህ በኋላ ያ ንስር ተነሣ፤ በጥ​ፍ​ሮ​ቹም ቆመ፤ በታ​ላቅ ድም​ፅም ጮኸ፤ ክን​ፎ​ቹ​ንም እን​ዲህ አላ​ቸው፦

8 “በየ​ቦ​ታ​ችሁ ተኙ እንጂ ሁላ​ችሁ እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ችሁ በአ​ን​ድ​ነት አት​ነሡ፤ በየ​ጊ​ዜ​ውም ትነ​ሣ​ላ​ችሁ።

9 የኋ​ለ​ኛ​ዪቱ ራሱም ከሁሉ ትበ​ል​ጣ​ለች።”

10 ባየሁ ጊዜም ድምፁ የሚ​ወጣ ከሥ​ጋው መካ​ከል እንጂ ከራሱ ውስጥ አይ​ደ​ለም።

11 የእ​ነ​ዚያ ራሶች ቍጥ​ሮ​ችም ስም​ንት ናቸው።

12 ከዚህ በኋላ በቀኝ በኩል ክንፍ ወጣ፤ ምድ​ሩ​ንም ሁሉ ገዛ።

13 ከዚህ በኋላ ጥፋቱ በደ​ረሰ ጊዜ ቦታው እስ​ከ​ማ​ይ​ታይ ድረስ እር​ሱም ጠፋ፤ ሁለ​ተ​ኛ​ውም ወጣ፤ እር​ሱም ብዙ ዘመን አጽ​ንቶ ገዛ።

14 ከዚ​ህም በኋላ ጥፋቱ በደ​ረሰ ጊዜ እር​ሱም እንደ ፊተ​ኛው ጠፋ።

15 ቃልም መጣ​ለት፤ እን​ዲ​ህም አለው፦

16 “ምድ​ርን ይህን ያህል ዘመን አጽ​ን​ተህ የም​ት​ገዛ አንተ ንስር ሳት​ጠፋ ይኽን የም​ነ​ግ​ር​ህን ስማ።

17 ከአ​ንተ በኋላ እንደ አንተ የሚ​ጸና፥ የእ​ኩ​ሌ​ታ​ህ​ንም ያህል የሚ​ገዛ የለም።”

18 ሦስ​ተ​ኛ​ውም ወጣ፤ እር​ሱም እንደ መጀ​መ​ሪ​ያው አጽ​ንቶ ገዛ፤ ከዚህ በኋላ እር​ሱም ጠፋ።

19 ከዚ​ህም በኋላ ዳግ​መኛ ክን​ፎቹ ሁሉ ወጡ፤ እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ቸ​ውም ገዙ፤ ዳግ​መኛ ሁሉም ጠፉ።

20 ከዚህ በኋላ ክን​ፎቹ አጽ​ን​ተው ይገዙ ዘንድ በግራ በኩል በየ​ጊ​ዜ​ያ​ቸው ተነሡ፤ ነገር ግን ፈጥ​ነው ጠፉ።

21 ከእ​ነ​ር​ሱም ውስጥ የተ​ነሡ አሉ፤ ነገር ግን እነ​ርሱ አል​ገ​ዙም።

22 ከዚህ በኋ​ላም እነ​ዚያ ዐሥራ ሁለቱ ክን​ፎቹ ጠፉ፤ እኒ​ያም ሁለቱ ራሶቹ ጠፉ።

23 ዝም ከሚሉ ከሦ​ስቱ ራሶ​ቹና ከስ​ድ​ስቱ ራሶቹ በቀር ከዚህ ንስር ወገን የቀረ የለም።

24 ከዚ​ህም በኋላ ከእ​ነ​ዚያ ከስ​ድ​ስቱ ራሶች ሁለቱ ተለ​ይ​ተው ሄዱ፤ በቀኝ በኩል ባለ ራሱ ውስ​ጥም ተቀ​መጡ፤ አራቱ ግን በቦ​ታ​ቸው ቀሩ።

25 እኒህ አራቱ ራሶች ግን ይቆሙ ዘንድ፥ እነ​ር​ሱም ይገዙ ዘንድ ተማ​ከሩ።

26 ከዚ​ህም በኋላ አንዱ ተነ​ሥቶ ቆመ፤ ነገር ግን ፈጥኖ ጠፋ።

27 ሁለ​ተ​ኛ​ውም እን​ዲሁ ከፊ​ተ​ኛው ይልቅ እርሱ ፈጥኖ ጠፋ።

28 ከዚህ በኋላ የቀ​ሩት እኒህ ሁለቱ ተተ​ክ​ተው ይገዙ ዘንድ እን​ዲሁ ተማ​ከሩ።

29 ከዚ​ህም በኋላ እኒህ ሲማ​ከሩ ዝም ከሚሉ ከሦ​ስቱ ራሶች መካ​ከ​ለኛ የሚ​ሆን አንዱ ተነሣ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም የሚ​በ​ልጥ እርሱ ነው።

30 ከዚ​ህም በኋላ እኒ​ህን ሁለ​ቱን ራሶች ከእ​ርሱ ጋር ወሰ​ዳ​ቸው።

31 ያም ራስ አብ​ረ​ውት ካሉት ጋራ ተመ​ለሰ፤ ይገዙ ዘንድ የተ​ማ​ከሩ እኒ​ህን ሁለ​ቱ​ንም ራሶች ዋጣ​ቸው።

32 ያም ራስ ምድ​ርን ሁሉ ያዛት፤ በው​ስ​ጥ​ዋም የሚ​ኖ​ሩ​ትን በብዙ ድካ​ምና መከራ አሠ​ቃ​ያ​ቸው፤ ከቆ​ሙት ከእ​ኒያ ክን​ፎች ሁሉ ይልቅ ፈጽሞ ዓለ​ምን ቀማ።

33 ከዚ​ህም በኋላ መካ​ከ​ለ​ኛው ራስ እንደ እነ​ዚያ ጠፋ።

34 ሁለቱ ራሶ​ችም ቀሩ፤ እነ​ር​ሱም እን​ዲሁ ምድ​ር​ንና በው​ስጧ የሚ​ኖ​ሩ​ትን ገዙ።

35 ከዚህ በኋላ ያ በቀኝ በኩል ያለው ራስ በግራ በኩል ያለ​ውን ዋጠው።


ከዱር የወጣ አን​በሳ

36 “ወደ ፊትህ ተመ​ል​ከት፤ የም​ታ​የ​ው​ንም ዕወቅ” የሚ​ለ​ኝን ቃል ሰማሁ።

37 ባየ​ሁም ጊዜ እነሆ አን​በሳ እያ​ገሣ ከዱር ተነሣ፤ እንደ ሰውም ድምፅ ሲና​ገር ሰማ​ሁት፤ ያንም ንስር እን​ዲህ አለው፦

38 “የም​ነ​ግ​ር​ህ​ንና ልዑል ያለ​ህን አንተ ስማ።

39 ምድ​ርን ይገ​ዟት ዘንድ ከፈ​ጠ​ር​ኋ​ቸው፥ የዘ​መ​ንም ፍጻሜ ከሚ​ደ​ር​ስ​ባ​ቸው ከእ​ነ​ዚያ ከአ​ራቱ እን​ስሳ የቀ​ረህ አንተ አይ​ደ​ለ​ህ​ምን?”

40 አራ​ተ​ኛ​ውም መጥቶ ያለ​ፉ​ትን በብዙ ድካ​ምና ሕማም ይህን ዓለም የቀ​ሙ​ትን እነ​ዚ​ያን እን​ስሳ ሁሉ ድል ያደ​ር​ጋ​ቸ​ዋል፤ ይህን ያህል ዘመን በዚህ ዓለም በተ​ን​ኰል ኖረ።

41 ዓለ​ም​ንም በክፉ አገ​ዛዝ ገዛት።

42 ጻድ​ቃ​ንን ቀም​ቶ​አ​ቸ​ዋ​ልና፥ ደጋ​ጎ​ቹ​ንም በድ​ሎ​አ​ቸ​ዋ​ልና፥ ቅኖ​ቹ​ንም ጠል​ቶ​አ​ቸ​ዋ​ልና፥ አሰ​ተ​ኞ​ቹ​ንም ወዶ​አ​ቸ​ዋ​ልና፥ የጻ​ድ​ቃ​ን​ንም አን​ባ​ቸ​ውን አፍ​ር​ሶ​አ​ልና፥ ያል​በ​ደ​ሉ​ት​ንም ቅጽ​ራ​ቸ​ውን አፍ​ር​ሶ​አ​ልና።

43 ኀጢ​አ​ቱም ወደ ልዑል ደር​ሳ​ለ​ችና፥ ትዕ​ቢ​ቱም ወደ ኀያል ደር​ሳ​ለ​ችና።

44 ልዑ​ልም የራ​ሱን ሰዎች ተመ​ል​ክ​ት​ዋ​ቸ​ዋ​ልና፥ እነ​ሆም ዓመቱ ተፈ​ጽ​ሞ​አ​ልና።

45 ስለ​ዚ​ህም አንተ ንስር ፈጽ​መህ ትጠ​ፋ​ለህ፤ ኀጢ​አ​ተ​ኞች ክን​ፎ​ችህ፥ ዝን​ጉ​ዎች ራሶ​ችህ፥ ክፉ​ዎች ጥፍ​ሮ​ች​ህና ዐመ​ፀ​ኛው ሥጋህ ይጠ​ፋሉ።

46 ምድ​ርም ከመ​ከ​ራዋ ሁሉ እፎይ ብላ ካንተ ፈጽማ ታርፍ ዘንድ የፈ​ጣ​ሪ​ዋን ፍር​ዱ​ንና ቸር​ነ​ቱን ተስፋ ታደ​ር​ጋ​ለች።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች