Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽሐፈ ዮዲት 3 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

1 ስለዚህ ሰላምን የሚለምኑ መልዕክተኞችን እንዲህ በማለት ላኩበት፦

2 “እነሆ፥ እኛ የታላቁ ንጉሥ የናቡከደነፆር አገልጋዮች በፊትህ እጅ እንነሣለን፥ በፊትህ እንደ ወደድህ አድርገን።

3 እነሆ መኖሪያዎቻችን፥ መሬታችን ሁሉ፥ እርሻዎቻችን፥ መንጋዎቻችን፥ በጐቻችንና የመሰማሪያችን ቦታዎች ሁሉ፥ በፊትህ ናቸው፤ እንደ ወደድህ አድርጋቸው።

4 እነሆ ከተሞቻችንና የሚኖሩባቸውም ሁሉ ባርያዎችህ ናቸው። መጥተህም ለዓይንህ መልካም የሆነውን አድርግ።”

5 ሰዎቹ ወደ ሆሎፎርኒስ መጥተው ይህንኑ ነገሩት።

6 እርሱም ከሠራዊቱ ጋር ወደ ባሕሩ ጠረፍ ወርደ፥ በተመሸጉት ከተሞችም የጦር ሰፈር አቆመ፤ እንዲረዱትም ከእነርሱ የተመረጡ ሰዎችን ወሰደ።

7 እነሱና በዙሪያውም ያሉ አገሮች ሁሉ አክሊል ደፍተው በጭፈራና በከበሮ ተቀበሉት።

8 እርሱ ግን አገራቸውን ሁሉ አጠፋ፥ የማምለኪያ ዐፀዶቻቸውንም ቆረጠ፤ ሕዝቦች ሁሉ ናቡከደነፆርን ብቻ እንዲያመልኩና ቋንቋዎችና ነገዶች ሁሉ አምላክ ብለው እንዲጠሩት፥ የምድሪቱን አማልክት እንዲያጠፋ ታዝዞ ነበርና።

9 ከይሁዳ ተራሮች አንፃር በዶታን አጠገብ ወደሚገኝ ወደ ኤስድራሎን መጣ።

10 በጌባና በሲቶፖሊስ መካከል ሰፈረ፥ ለሠራዊቱ ስንቅ ለመሰብሰብ በዚያ አንድ ወር ሙሉ ተቀመጠ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች