Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -

ሕዝቅኤል 1 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዙፋን

1 በሠ​ላ​ሳ​ኛው ዓመት በአ​ራ​ተ​ኛው ወር ከወ​ሩም በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ቀን በኮ​ቦር ወንዝ በም​ር​ኮ​ኞች መካ​ከል ሳለሁ ሰማ​ያት ተከ​ፈቱ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ራእይ አየሁ።

2 ንጉሡ ዮአ​ኪን በተ​ማ​ረከ በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ዓመት፥ ከወ​ሩም በአ​ም​ስ​ተ​ኛው ቀን፥

3 የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል በከ​ለ​ዳ​ው​ያን ሀገር በኮ​ቦር ወንዝ ላይ ወደ ቡዝ ልጅ ወደ ካህኑ ወደ ሕዝ​ቅ​ኤል መጣ። የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እጅ በዚያ በእኔ ላይ ሆነች፤

4 እኔም አየሁ፤ እነ​ሆም ከሰ​ሜን በኩል ዐውሎ ነፋ​ስና ታላቅ ደመና፥ የሚ​በ​ር​ቅም እሳት መጣ፤ በዙ​ሪ​ያ​ውም ፀዳል ነበረ፤ በመ​ካ​ከ​ልም በእ​ሳቱ ውስጥ የሚ​ብ​ለ​ጨ​ለጭ ነገር ነበረ።

5 ከመ​ካ​ከ​ልም የአ​ራት እን​ስ​ሶች አም​ሳያ ወጣ። መል​ካ​ቸ​ውም እን​ደ​ዚህ ነበረ፤ ሰውም ይመ​ስሉ ነበረ።

6 ለእ​ያ​ን​ዳ​ን​ዱም አራት አራት ፊት፥ ለእ​ያ​ን​ዳ​ን​ዱም አራት አራት ክንፍ ነበ​ሩት።

7 እግ​ሮ​ቻ​ቸ​ውም ቀጥ ያሉ ነበሩ፤ የእ​ግ​ራ​ቸው ሰኰና እንደ ላም እግር ሰኰና ነበረ፤ እንደ ተወ​ለ​ወለ ናስም ይብ​ለ​ጨ​ለጭ ነበር።

8 በክ​ን​ፎ​ቻ​ቸ​ውም በታች በእ​የ​አ​ራቱ ጐድ​ና​ቸው የሰው እጅ ነበረ፤ ለአ​ራ​ቱም እን​ደ​ዚህ ያሉ ፊትና ክንፍ ነበ​ሩ​አ​ቸው።

9 የሁ​ሉም ክን​ፎ​ቻ​ቸው አንዱ ከአ​ንዱ ጋር የተ​ያ​ያዘ ነው፤ ሲሄ​ዱም ወዲ​ያና ወዲህ ሳይሉ አቅ​ን​ተው ይሄ​ዳሉ፤ አን​ዱም አን​ዱም ወደ​ፊቱ ይሄ​ዳል።

10 የፊ​ታ​ቸው አም​ሳያ እን​ደ​ዚህ ነው፦ ለአ​ራቱ ሁሉ በቀ​ኛ​ቸው የሰው ፊትና የአ​ን​በሳ ፊት አላ​ቸው፤ ለአ​ራ​ቱም ሁሉ በግ​ራ​ቸው የእ​ን​ስሳ ፊትና የን​ስር ፊት አላ​ቸው።

11 ክን​ፋ​ቸ​ውም በላይ ተዘ​ር​ግቶ ነበር፤ የእ​ያ​ን​ዳ​ን​ዱም ሁለት ሁለት ክን​ፋ​ቸው የተ​ያ​ያዙ ነበሩ፤ ሁለት ሁለ​ቱም ገላ​ቸ​ውን ይከ​ድኑ ነበር።

12 እያ​ን​ዳ​ን​ዱም ወደ ፊት ቀጥ ብሎ ይሄድ ነበር፤ መን​ፈ​ስም ወደ​ሚ​ሄ​ድ​በት ሁሉ ይሄዱ ነበር፤ ሲሄ​ዱም ወዲ​ያና ወዲህ አይ​ሉም ነበር።

13 በእ​ን​ስ​ሶ​ቹም መካ​ከል እን​ደ​ሚ​ነ​ድድ የእ​ሳት ፍም ያለ አም​ሳያ ነበረ፤ በእ​ን​ስ​ሶቹ መካ​ከል ወዲ​ህና ወዲያ የሚ​ሄድ እንደ ፋና ያለ አም​ሳያ ነበረ፤ ለእ​ሳ​ቱም ፀዳል ነበ​ረው፤ ከእ​ሳ​ቱም መብ​ረቅ ይወጣ ነበር።

14 እን​ስ​ሶ​ቹም እንደ መብ​ረቅ አም​ሳያ ይሮ​ጡና ይመ​ለሱ ነበር።

15 ስመ​ለ​ከ​ትም፥ እነሆ በአ​ራቱ እን​ስ​ሶች አጠ​ገብ በም​ድር ላይ አንድ መን​ኰ​ራ​ኵር አየሁ።

16 የመ​ን​ኰ​ራ​ኵ​ሩም መልክ እንደ ቢረሌ ነበረ፤ አራ​ቱም አንድ አም​ሳያ ነበሩ፤ ሥራ​ቸ​ውም በመ​ን​ኰ​ራ​ኵር ውስጥ እን​ዳለ መን​ኰ​ራ​ኵር ነበረ።

17 በእ​የ​አ​ራ​ቱም ጐድ​ና​ቸው ይሄዱ ነበር፤ ሲሄ​ዱም ጀር​ባ​ቸ​ውን አይ​መ​ል​ሱም ነበር። ከፍ ከፍ ያሉም ነበሩ።

18 በአ​ራቱ ዙሪያ ሁሉ ዐይ​ኖ​ችን የተ​መላ ጀር​ባ​ቸ​ውን አየሁ፤

19 በሄ​ዱም ጊዜ ሠረ​ገ​ላ​ዎች ከእ​ነ​ርሱ ጋር ይሄ​ዳሉ። እን​ስ​ሶ​ቹም ከም​ድር ሲነሡ መን​ኰ​ራ​ኵ​ሮ​ቹም ከእ​ነ​ርሱ ጋር ይነ​ሣሉ።

20 ደመና ባለ​በት በዚያ መን​ፈስ አለ፤ እን​ስ​ሶቹ ይሄ​ዳሉ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር መን​ኰ​ራ​ኵ​ሮቹ ይነ​ሣሉ፤ የሕ​ይ​ወት መን​ፈስ በመ​ን​ኰ​ራ​ኵ​ሮች አለና።

21 በሄ​ዱም ጊዜ ይሄ​ዳሉ፤ በቆ​ሙም ጊዜ ይቆ​ማሉ፤ በእ​ነ​ዚያ መን​ኰ​ራ​ኵ​ሮች ውስጥ የሕ​ይ​ወት መን​ፈስ አለና ከም​ድር በተ​ነሡ ጊዜ መን​ኰ​ራ​ኵ​ሮቹ ከእ​ነ​ርሱ ጋር ይነ​ሣሉ።

22 በእ​ነ​ዚያ እን​ስ​ሶች ራስ ላይ ያለው መልክ ከላይ በክ​ን​ፎ​ቻ​ቸው ላይ የተ​ዘ​ረጋ የበ​ረድ መልክ እን​ዳ​ለ​በት ጠፈር ነው፤

23 ከጠ​ፈ​ሩም በታች ክን​ፎ​ቻ​ቸው እርስ በር​ሳ​ቸው ተቃ​ን​ተው ነበር፤ ለእ​ያ​ን​ዳ​ን​ዱም ገላ​ውን የሚ​ከ​ድኑ ሁለት ሁለት ክን​ፎች ነበ​ሩት።

24 ሲሄ​ዱም የክ​ን​ፎ​ቻ​ቸው ድምፅ እንደ ብዙ ውኃ ድምፅ፥ ሁሉን እን​ደ​ሚ​ችል የአ​ም​ላ​ክም ድምፅ፥ እንደ ታላቅ ሠራ​ዊ​ትም ድምፅ ሆኖ ሰማሁ፤ ሲቆ​ሙም ክን​ፎ​ቻ​ቸ​ውን ይሰ​በ​ስቡ ነበር።

25 በራ​ሳ​ቸ​ውም ላይ ካለው ጠፈር በላይ ድምፅ ተሰማ፤ ሲቆ​ሙም ክን​ፎ​ቻ​ቸ​ውን ይሰ​በ​ስቡ ነበር።

26 በራ​ሳ​ቸ​ውም በላይ ከአ​ለው ጠፈር በላይ የሰ​ን​ፔር ድን​ጋይ የሚ​መ​ስል የዙ​ፋን አም​ሳያ ነበረ፤ በዙ​ፋ​ኑም አም​ሳያ ላይ እንደ ሰው መልክ አም​ሳያ ነበረ።

27 ከወ​ገ​ቡም አም​ሳያ ወደ ላይ የሚ​ብ​ለ​ጨ​ለጭ የወ​ርቅ አም​ሳያ አየሁ፤ ከወ​ገ​ቡም አም​ሳያ ወደ ታች እንደ እሳት አም​ሳያ አየሁ፤ በዙ​ሪ​ያ​ውም ፀዳል ነበረ።

28 በዝ​ናብ ቀን በደ​መና ውስጥ እንደ አለ ቀስተ ደመና አም​ሳያ፥ እን​ዲሁ በዙ​ሪ​ያው ያለ ፀዳል አም​ሳያ ነበረ። የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ክብር ምሳሌ መልክ ይህ ነበረ። በአ​የ​ሁም ጊዜ በግ​ን​ባሬ ተደ​ፋሁ። የሚ​ና​ገ​ር​ንም ድምፅ ሰማሁ።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች