ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ መጽሐፈ ጦቢት 10:7 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)7 እርሷም አለችው፥ “አንተም ዝም በል፤ አታታለኝ፤ ልጄስ ሞትዋል።” ታለቅስለትም ዘንድ በሄደበት ጎዳና ሁልጊዜ ትሄድ ነበር። የሰርጉ በዓል ሳያልቅ እንዳይሄድ ራጉኤል ያማለው ዐሥራ አራቱ የበዐዓል ቀን እስኪፈጸም ድረስ ለልጅዋ ለጦብያ እያለቀሰችለት በቀን እህል አትበላም ነበር፤ በሌሊትም ዝም አትልም ነበር። ምዕራፉን ተመልከትመጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)7 አሁን በቅርቡ ይመጣል።” እርሷ ግን “ተወኝ፥ እኔን ማታለል ይቅርብህ፥ ሞቷል” በማለት መሰለችለት። ዓይኗን እንጂ ማንንም ስለማታምን ልጇ የሄደበትን መንገድ ለመመልከት በየቀኑ ፈጥና ትወጣ ነበር። ፀሃይ ስትጠልቅ ወደ ቤትዋ ትመለስ ነበር፤ ሌሊቱን ሙሉ እያዘነችና እያለቀሰች ታድር ነበር፥ እንቅፍል አይወስዳትም ነበር። ራጉኤል ለልጁ ሲል ምሎ የወሰናቸው ዐሥራ አራት የሰርግ ቀኖች እንዳልፉ፥ ጦብያ ወደ እርሱ ሄደና እንዲህ አለው “እንድሄድ ፍቀድልኝ አባትና እናቴ ከእንግዲህ ወዲህ አናየውም ብለው ተስፋ ቆርጠው ይሆናል፤ ስለዚህ እባክህ አባቴ እንድሄድ ፍቀድልኝ፥ ወደ አባቴ ቤት ልመለስ፥ በምን ሁኔታ ላይ እንደተውኩት አስቀድሜ ነግሬሃለሁ።” ምዕራፉን ተመልከት |