Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -




ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ጦቢት 10:12 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

12 እር​ሱም፥ “ልጆች ሆይ፥ ሳል​ሞት የሰ​ማይ ጌታ በጎ ነገር ያድ​ር​ግ​ላ​ችሁ” ብሎ መረ​ቃ​ቸው፤ ልጁ​ንም እን​ዲህ አላት፥ “አማ​ቶ​ች​ሽን አክ​ብሪ፤ እን​ግ​ዲህ ወዲህ ዘመ​ዶ​ችሽ እነ​ርሱ ናቸ​ውና፤ እኛም በአ​ንቺ መል​ካ​ሙን እን​ስማ” ብሎ ሳማት። አድ​ናም ጦብ​ያን አለ​ችው፥ “አንተ የም​ወ​ድህ ወን​ድሜ ሆይ፥ የሰ​ማይ ጌታ ከልጄ ከሣራ ልጆ​ችን ሰጥ​ቶህ አይ​ልህ ዘንድ፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት ደስ ይለኝ ዘንድ ጎዳ​ና​ህን ያቅ​ና​ልህ። እነሆ፥ ልጄን አደራ ሰጥ​ቼ​ሃ​ለሁ፤ አታ​ሳ​ዝ​ናት።”

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

12 ልጁን ሣራንም እንዲህ አላት “አማቾችሽን አክብሪያቸው፥ ምክንያቱም ከእንግዲህ ወዲህ ከወለዱሽ ይልቅ ወላጆች የሚሆኑሽ እነሱ ናቸውና፤ በሰላም ሂጂ ልጄ፥ በሕይወቴ ሳለሁ ስለ አንቺ መልካም ወሬ ብቻ ያሰማኝ።” ተሰናበታቸውና ሸኛቸው። ኤድናም በተራዋ ጦብያን እንዲህ አለችው “እጅግ የተወደድህ ልጄና ወንድሜ፥ ጌታ በደኀና ይመልስህ፥ እኔም ከመሞቴ በፊት ያንተንና የልጄን የሣራን ልጆች ለማየት ያብቃኝ፤ በጌታ ፊት ልጄን እንድትጠብቃት ለአንተ አስረክባታለሁ፤ በሕይወትህ ዘመን ሁሉ ምንጊዜም አታሣዝናት፤ በሰላም ሂዱ ልጄ፤ ከእንግዲህ ወዲህ እኔ እናትህ ነኝ፥ ሣራ ደግም እኀትህ ናት። ሁላችንም በሕይወት ዘመናችን ሁሉ በደስታ ያኑረን።” ከዚህ በኋላ ሁለቱንም ሳመቻቸውና በደስታ ሸኘቻቸው።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ




መጽ​ሐፈ ጦቢት 10:12
0 ተሻማሚ ማመሳሰሪያዎች  

ተከተሉን:

ማስታወቂያዎች


ማስታወቂያዎች