ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ መጽሐፈ ጦቢት 1:4 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)4 እኔም ሕፃን ሆኜ ከእስራኤል ልጆች ጋር በሀገሬ ሳለሁ የአባቴ የንፍታሌም ወገኖች ሁሉ፥ እስራኤልም ሁሉ በእርሷ ይሠዉ ዘንድ እግዚአብሔር ከእስራኤል ነገድ ሁሉ ከመረጣት የልዑል ቤተ መቅደስ ለትውልድ ሁሉ ለዘለዓለም ከታነጸባትና ከተቀደሰባት ከኢየሩሳሌም ወጥተው ካዱ። ምዕራፉን ተመልከትመጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)4 በአገሬ እስራኤል ምድር በነበርኩበት ጊዜና ገና ወጣት ሳለሁ፥ የአባቶቼ የናፍታሊ ወገኖች በሙሉ የዳዊትን ቤትና ኢየሩሳሌምን ጥለው ሄዱ። ይህች ከተማ ከእስራኤል ነገዶች በሙሉ ተመርጣ፥ የእግዚአብሔር ማደሪያ በሆነው በቤተ መቅደሱ፥ የእስራኤል ነገዶች መሥዋዕት እንዲያቀርቡባት፥ ለትውልድ ሁሉ ለዘለዓለም ተቀድሳና ታንፃ ነበር። ምዕራፉን ተመልከት |