ምሳሌ 12:23 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)23 ብልህ ሰው የጥበብ መንበር ነው፤ የሰነፎች ልብ ግን መርገምን ያገኛል። ምዕራፉን ተመልከትአዲሱ መደበኛ ትርጒም23 አስተዋይ ሰው ዕውቀቱን ይሰውራል፤ የሞኞች ልብ ግን ቂልነትን ይነዛል። ምዕራፉን ተመልከትመጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)23 ብልህ ሰው እውቀትን ይሸሽጋል፥ የሰነፎች ልብ ግን ስንፍናን ያወራል። ምዕራፉን ተመልከትአማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም23 አስተዋይ ሰዎች “ዐዋቂዎች ነን” እያሉ አይመጻደቁም፤ ሞኞች ግን “ዐዋቂዎች ነን” በማለት ድንቊርናቸውን ይገልጣሉ። ምዕራፉን ተመልከት |