Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -




ኢያሱ 10:40 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

40 እን​ዲ​ሁም ኢያሱ ምድ​ሪ​ቱን ሁሉ፥ ተራ​ራ​ማ​ውን ሀገር፥ ደቡ​ቡ​ንም፥ ቆላ​ው​ንም፥ ቍል​ቍ​ለ​ቱ​ንም፥ ንጉ​ሦ​ቻ​ቸ​ው​ንም ሁሉ መታ፤ ማን​ንም አላ​ስ​ቀ​ረም፤ የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዳ​ዘ​ዘ​ውም ነፍስ ያለ​በ​ትን ሁሉ ፈጽሞ አጠፋ።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

40 በዚህ ሁኔታም ኢያሱ ተራራማውን አገር ኔጌብን፣ የምዕራቡን ቈላና የተራራውን ሸንተረሮች ጨምሮ ምድሪቱን በሙሉ ከነገሥታቷ ጋራ ያዘ። የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ባዘዘውም መሠረት፣ እስትንፋስ ያላቸውን ሁሉ ፈጽሞ ደመሰሰ፤ ማንንም በሕይወት አላስቀረም።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

40 እንዲሁም ኢያሱ ምድሪቱን ሁሉ ተራራማውን አገር ደቡቡንም ቈላውንም የተዳፋቱንም ስፍራ ነገሥታቶቻቸውንም ሁሉ መታ፤ ማንንም አላስቀረም፤ የእስራኤል አምላክ ጌታ እንዳዘዘውም እስትንፋስ ያለውንም ሁሉ ፈጽሞ አጠፋ።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

40 በዚህ ዐይነት ኢያሱ ምድሪቱን በሙሉ፥ የተራራማውን አገር፥ ኔጌብን፥ የተራራውን ቊልቊለትና ነገሥታቱን ሁሉ ያዘ፤ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ባዘዘው መሠረት ሁሉንም ፈጀ እንጂ አንድ ሰው እንኳ በሕይወት እንዲኖር አላስተረፈም።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

40 እንዲሁም ኢያሱ ምድሪቱን ሁሉ ተራራማውን አገር ደቡቡንም ቈላውንም ቁልቁለቱንም ነገሥታቶቻቸውንም ሁሉ መታ፥ ማንንም አላስቀረም፥ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዳዘዘውም ነፍስ ያለበትን ሁሉ ፈጽሞ አጠፋ።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ




ኢያሱ 10:40
26 ተሻማሚ ማመሳሰሪያዎች  

ከነ​ገ​ሠም በኋላ የኢ​ዮ​ር​ብ​ዓ​ምን ወገን ሁሉ አጠፋ፥ በባ​ሪ​ያው በሴ​ሎ​ና​ዊው በአ​ኪያ እጅ እንደ ተና​ገ​ረው እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል፥ እስ​ኪ​ያ​ጠ​ፋው ድረስ ከኢ​ዮ​ር​ብ​ዓም ወገን ሕይ​ወት ያለ​ውን አላ​ስ​ቀ​ረም።


እነ​ር​ሱም ወረ​ሱ​አት፤ በከ​ነ​ዓን ምድር የሚ​ኖ​ሩ​ት​ንም ሰዎች በፊ​ታ​ቸው አጠ​ፋ​ሃ​ቸው፤ የሚ​ወ​ድ​ዱ​ት​ንም ነገር ያደ​ር​ጉ​ባ​ቸው ዘንድ እነ​ር​ሱ​ንና ነገ​ሥ​ታ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን፥ የም​ድ​ሩ​ንም አሕ​ዛብ በእ​ጃ​ቸው አሳ​ል​ፈህ ሰጠ​ሃ​ቸው።


ኀጢ​አ​ተ​ኞች ወደ ሲኦል ይመ​ለሱ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ረሱ አሕ​ዛ​ብም ሁሉ።


በመ​ካ​ከ​ልህ ወጥ​መድ እን​ዳ​ይ​ሆ​ኑ​ብህ አንተ በም​ት​ገ​ባ​በት ምድር ከሚ​ኖሩ ሰዎች ጋር ቃል ኪዳን እን​ዳ​ታ​ደ​ርግ ተጠ​ን​ቀቅ፤


ሙሴም የከ​ነ​ዓ​ንን ምድር ይሰ​ልሉ ዘንድ ላካ​ቸው፤ አላ​ቸ​ውም፥ “ከዚህ ወደ ምድረ በዳ ሂዱ፥ ወደ ተራ​ሮ​ችም ውጡ።


ተመ​ል​ሳ​ችሁ ተጓዙ፤ ወደ አሞ​ራ​ው​ያን ተራራ፥ ወደ አረ​ባም ሀገ​ሮች ሁሉ፥ በተ​ራ​ራ​ውም፥ በሜ​ዳ​ውም፥ በሊ​ባም፥ በባ​ሕ​ርም ዳር ወዳሉ ወደ ከነ​ዓ​ና​ው​ያን ምድር፥ ወደ ሊባ​ኖ​ስም ፊት ለፊት እስከ ታላቁ ወንዝ እስከ ኤፍ​ራ​ጥስ ድረስ ሂዱ።


በዚ​ያን ጊዜም ከተ​ሞ​ቹን ሁሉ ወሰ​ድን፤ ከተ​ማ​ው​ንም ሁሉ፥ ሴቶ​ች​ንም፥ ሕፃ​ኖ​ች​ንም አጠ​ፋን፤ አን​ዳ​ችም የሸሸ በሕ​ይ​ወት አላ​ስ​ቀ​ረ​ንም፥


ነገ​ሥ​ታ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም በእ​ጅህ አሳ​ልፎ ይሰ​ጣ​ቸ​ዋል፤ ስማ​ቸ​ው​ንም ከዚያ ቦታ ያጠ​ፋል፤ እስ​ክ​ታ​ጠ​ፋ​ቸው ድረስ ማንም ከፊ​ትህ ይቆም ዘንድ አይ​ች​ልም።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በእ​ስ​ር​ኤል እጅ አሳ​ልፎ ሰጣት፤ በዚ​ያም ቀን ያዙ​አት፤ በሰ​ይ​ፍም ስለት መቱ​አት፤ በላ​ኪ​ስም እን​ዳ​ደ​ረ​ገው ሁሉ፥ በእ​ር​ስዋ ያሉ​ትን ነፍ​ሳት ሁሉ ፈጽሞ አጠፋ።


እር​ስ​ዋ​ንም፥ ንጉ​ሥ​ዋ​ንም፥ ከተ​ሞ​ች​ዋ​ንም ሁሉ፥ በእ​ር​ስ​ዋም ያሉ​ትን ነፍ​ሳት ሁሉ በሰ​ይፍ ስለት መቱ፤ በአ​ዶ​ላም እን​ዳ​ደ​ረ​ገው ሁሉ ማን​ንም አላ​ስ​ቀ​ረም ፤ እር​ስ​ዋ​ንም፥ በእ​ር​ስ​ዋም ያሉ​ትን ነፍ​ሳት ሁሉ ፈጽሞ አጠፋ።


እር​ስ​ዋ​ንም፥ ንጉ​ሥ​ዋ​ንም፥ ከተ​ሞ​ች​ዋ​ንም ያዙ፤ በሰ​ይ​ፍም ስለት መቱ​አ​ቸው፤ በእ​ነ​ር​ሱም ውስጥ ያሉ​ትን ነፍ​ሳት ሁሉ ፈጽ​መው አጠፉ፤ ማን​ንም አላ​ስ​ቀ​ረም፤ በኬ​ብ​ሮ​ንና በን​ጉ​ሥ​ዋም እን​ዳ​ደ​ረ​ገው እን​ዲሁ በዳ​ቤ​ርና በን​ጉ​ሥዋ አደ​ረገ።


ኢያ​ሱም ያን ምድር ሁሉ፥ ተራ​ራ​ማ​ውን፥ ደቡ​ቡ​ንም ሁሉ፥ የጎ​ሶ​ም​ንም ምድር ሁሉ ፥ ሜዳ​ው​ንም፥ በም​ዕ​ራብ በኩል ያለ​ው​ንም፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ተራ​ራ​ማ​ው​ንና ቆላ​ውን ያዘ፤


በተ​ራ​ራና በሜዳ በዓ​ረባ፥ በአ​ሴ​ዶት በቆ​ላው፥ በና​ጌብ፥ በኬ​ጤ​ዎ​ንና በአ​ሞ​ሬ​ዎን፥ በከ​ና​ኔ​ዎ​ንና በፌ​ር​ዜ​ዎን፥ በኢ​ያ​ቡ​ሴ​ዎ​ንና በኤ​ዌ​ዎን ያለ ርስ​ታ​ቸ​ውን አወ​ረ​ሳ​ቸው።


የብ​ን​ያ​ምም ልጆች ነገድ ከተ​ሞች በየ​ወ​ገ​ኖ​ቻ​ቸው እነ​ዚህ ነበሩ፤ ኢያ​ሪኮ፥ ቤት​ሖ​ግሊ፥ ዐመ​ቀ​ስስ፤


ከተ​ማ​ዪ​ቱም በእ​ር​ስ​ዋም ያለው ሁሉ ለሠ​ራ​ዊት ጌታ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እርም ይሆ​ናሉ፤ የላ​ክ​ና​ቸ​ውን መል​እ​ክ​ተ​ኞች ስለ ሸሸ​ገች ዘማ​ዊቱ ረዓብ፥ ከእ​ር​ስ​ዋም ጋር በቤቷ ውስጥ ያሉ ሁሉ ብቻ በሕ​ይ​ወት ይኖ​ራሉ።


በኢ​ያ​ሪ​ኮና በን​ጉ​ሥ​ዋም እን​ዳ​ደ​ረ​ግህ እን​ዲሁ በጋ​ይና በን​ጉ​ሥዋ ታደ​ር​ጋ​ለህ፤ የከ​ብ​ቱን ምርኮ ግን ለራ​ሳ​ችሁ ትዘ​ር​ፋ​ላ​ችሁ፤ ከከ​ተ​ማ​ዪ​ቱም በስ​ተ​ኋላ ይከ​ብ​ቧት ዘንድ ጦር ላክ” አለው።


ነገር ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ኢያ​ሱን እን​ዳ​ዘ​ዘው የዚ​ያ​ችን ከተማ ከብ​ትና ምርኮ ሁሉ የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ለራ​ሳ​ቸው ዘረፉ፤


መል​ሰ​ውም ኢያ​ሱን፥ “እኛ ባሪ​ያ​ዎ​ችህ ምድ​ሪ​ቱን ሁሉ ይሰ​ጣ​ችሁ ዘንድ፥ በእ​ር​ስ​ዋም የሚ​ኖ​ሩ​ትን ሁሉ ከፊ​ታ​ችሁ ያጠፋ ዘንድ አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ባሪ​ያ​ውን ሙሴን እን​ዳ​ዘዘ በእ​ው​ነት ሰም​ተ​ናል፤ ስለ​ዚ​ህም ከእ​ና​ንተ የተ​ነሣ ስለ ነፍ​ሳ​ችን እጅግ ፈራን፤ ይህ​ንም ነገር አድ​ር​ገ​ናል፤


ተከተሉን:

ማስታወቂያዎች


ማስታወቂያዎች