Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ

- ማስታወቂያዎች -




ዘፀአት 30:31 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

31 አን​ተም ለእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች እን​ዲህ ብለህ ተና​ገር፤ ይህ ለልጅ ልጃ​ችሁ የተ​ቀ​ደሰ የቅ​ብ​ዐት ዘይት ይሁን።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

31 ለእስራኤላውያን ንገራቸው፤ ‘በሚመጡት ትውልዶች ሁሉ ይህ የእኔ የተቀደሰ የቅብዐት ዘይት ይሆናል።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

31 የእስራኤልን ልጆች እንዲህ ብለህ ንገራቸው፦ ‘ይህ በትውልዳችሁ ሁሉ ለእኔ የተቀደሰ የቅባት ዘይት ነው።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

31 ለእስራኤልም ሕዝብ እንዲህ ብለህ ንገራቸው፤ ‘ይህ የተቀደሰ የቅባት ዘይት ለሚመጡት ዘመናት ሁሉ ለእኔ አገልግሎት ይዋል፤

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

31 አንተም ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ብለህ ተናገር፦ ይህ ለልጅ ልጃችሁ የተቀደሰ የቅብዓት ዘይት ይሁንልኝ።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ




ዘፀአት 30:31
7 ተሻማሚ ማመሳሰሪያዎች  

በመ​ሠ​ዊ​ያ​ውም ላይ ካለው ደም ከቅ​ብ​ዐት ዘይ​ትም ወስ​ደህ በአ​ሮ​ንና በል​ብሱ ላይ፥ ከእ​ር​ሱም ጋር ባሉት በል​ጆ​ቹና በል​ብ​ሶ​ቻ​ቸው ላይ ትረ​ጨ​ዋ​ለህ፤ እር​ሱም ልብ​ሶ​ቹም፥ ከእ​ር​ሱም ጋር ልጆቹ፥ ልብ​ሶ​ቻ​ቸ​ውም ይቀ​ደ​ሳሉ።


በክ​ህ​ነ​ትም ያገ​ለ​ግ​ሉኝ ዘንድ አሮ​ን​ንና ልጆ​ቹን ቅባ​ቸው፤ ቀድ​ሳ​ቸ​ውም።


በሌላ ሰው ሥጋ ላይ አይ​ፍ​ሰስ፤ እንደ እር​ሱም የተ​ሠራ ሌላ ቅብ​ዐት አታ​ድ​ርጉ፤ ቅዱስ ነው፤ ለእ​ና​ን​ተም ቅዱስ ይሁን።


የተ​ቀ​ደ​ሰ​ው​ንም የቅ​ብ​ዐ​ቱን ዘይት፥ ጥሩ​ው​ንም የጣ​ፋጭ ሽቱ ዕጣን በቀ​ማሚ ብል​ሃት እንደ ተሠራ አደ​ረገ።


“በራ​ሱም ላይ የቅ​ባት ዘይት የፈ​ሰ​ሰ​በት፥ የክ​ህ​ነ​ትም ልብስ ይለ​ብስ ዘንድ የተ​ቀ​ደሰ፥ ከወ​ን​ድ​ሞቹ የተ​ለ​የው ካህን ራሱን አይ​ላጭ፤ ልብ​ሱ​ንም አይ​ቅ​ደድ።


ከቅ​ብ​ዐ​ቱም ዘይት በአ​ሮን ራስ ላይ አፈ​ሰሰ፤ ቀባው፤ ቀደ​ሰ​ውም።


ተከተሉን:

ማስታወቂያዎች


ማስታወቂያዎች