Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -




2 ሳሙኤል 24:24 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

24 ንጉ​ሡም ኦር​ናን፥ “እን​ዲህ አይ​ደ​ለም፤ ነገር ግን በዋጋ ከአ​ንተ እገ​ዛ​ለሁ፤ ለአ​ም​ላ​ኬም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕት ያለ ዋጋ አላ​ቀ​ር​ብም” አለው። ዳዊ​ትም አው​ድ​ማ​ው​ንና በሬ​ዎ​ቹን በአ​ምሳ ሰቅል ብር ገዛ።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

24 ንጉሡ ግን ኦርናን፣ “እንዲህ አይደረግም፤ ዋጋውን ላንተ መክፈል አለብኝ፤ ለአምላኬም ለእግዚአብሔር የሚቃጠል መሥዋዕት ያለ ዋጋ አላቀርብም” አለው። ስለዚህም ዳዊት ዐውድማውንና በሬዎቹን በዐምሳ ሰቅል ብር ገዛ፤

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

24 ንጉሡ ግን ኦርናን፥ “መክፈል ያለብኝን ዋጋ ላንተ ከፍዬ እንጂ እንዲሁማ አይሆንም፤ ለጌታም ለአምላኬ የሚቃጠል መሥዋዕት ያለ ዋጋ አላቀርብም” አለው። ስለዚህም ዳዊት ዐውድማውንና በሬዎቹን በአምሳ ሰቅል ብር ገዛ፤

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

24 ንጉሥ ዳዊት ግን “ይህስ አይሆንም፤ ዋጋውን መክፈል አለብኝ፤ እኔ ምንም ዋጋ ያላወጣሁበትን ነገር ለአምላኬ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት አድርጌ ማቅረብ አይገባኝም” አለው፤ ከዚህም በኋላ ዳዊት አውድማውንና በሬዎቹን በኀምሳ ጥሬ ብር ገዛ፤

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

24 ንጉሡም ኦርናን፦ እንዲህ አይደለም፥ ነገር ግን በዋጋ ከአንተ እገዛለሁ፥ ለአምላኬም ለእግዚአብሔር የሚቃጠል መሥዋዕት ያለዋጋ አላቀርብም አለው። ዳዊትም አውድማውንና በሬዎቹን በአምሳ ሰቅል ብር ገዛ።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ




2 ሳሙኤል 24:24
8 ተሻማሚ ማመሳሰሪያዎች  

“አይ​ደ​ለም፥ ጌታዬ፥ ቀር​በህ ስማኝ፤ እር​ሻ​ውን፥ በው​ስ​ጡም ያለ​ውን ዋሻ​ውን ሰጥ​ቼ​ሃ​ለሁ፤ በወ​ገኔ ልጆች ፊት ሰጥ​ቼ​ሃ​ለሁ፤ ሬሳ​ህን ቅበር።”


የሀ​ገሩ ሕዝ​ብም ሲሰሙ ለኤ​ፍ​ሮን እን​ዲህ ሲል ተና​ገረ፥ “ከእኔ ቅርብ ነህና ስማኝ፤ የእ​ር​ሻ​ህ​ንም ዋጋ ከእኔ ውሰድ፤ ሬሳ​ዬ​ንም በዚያ እቀ​ብ​ራ​ለሁ።”


አብ​ር​ሃ​ምም የኤ​ፍ​ሮ​ንን ነገር ሰማ፤ አብ​ር​ሃ​ምም በኬጢ ልጆች ፊት የነ​ገ​ረ​ው​ንና ተቀ​ባ​ይ​ነት ያለ​ውን ግብዝ ያይ​ደለ አራት መቶ ምዝ​ምዝ ብር መዝኖ ለኤ​ፍ​ሮን ሰጠው።


ያን​ጊ​ዜም ሰይ​ጣን በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ ተነሣ፤ እስ​ራ​ኤ​ል​ንም ይቈ​ጥር ዘንድ ዳዊ​ትን አነ​ሣ​ሣው።


ዳዊ​ትም፥ “ይህ የአ​ም​ላኬ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ነው፤ ይህም ለእ​ስ​ራ​ኤል ለሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕት የሚ​ሆ​ነው መሠ​ዊያ ነው” አለ።


ክፉ ላደ​ረ​ገ​ባ​ች​ሁም ክፉ አት​መ​ል​ሱ​ለት፤ በሰው ሁሉ ፊት በጎ​ውን ተነ​ጋ​ገሩ።


ተከተሉን:

ማስታወቂያዎች


ማስታወቂያዎች