Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -




1 ሳሙኤል 25:1 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ሳሙ​ኤ​ልም ሞተ፤ እስ​ራ​ኤ​ልም ሁሉ ተሰ​ብ​ስ​በው አለ​ቀ​ሱ​ለት፤ በአ​ር​ማ​ቴ​ምም በቤቱ ቀበ​ሩት። ዳዊ​ትም ተነ​ሥቶ ወደ ማዖን ምድረ በዳ ወረደ።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

1 ሳሙኤልም ሞተ፤ እስራኤል ሁሉ ተሰብስበው አለቀሱለት፤ አርማቴም ባለው ቤቱም ቀበሩት። ከዚያም ዳዊት ተነሥቶ ወደ ፋራን ምድረ በዳ ወረደ።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

1 ሳሙኤልም ሞተ፤ መላው እስራኤል ሁሉ ተሰብስበው አለቀሱለት፤ ራማ ባለው ቤቱም ቀበሩት። ከዚያም ዳዊት ተነሥቶ ወደ ፋራን ምድረ በዳ ወረደ።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

1 ሳሙኤል ሞተ፤ መላው እስራኤላውያንም በአንድነት መጥተው አለቀሱለት፤ ከዚያም በኋላ በራማ በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ቀበሩት። ከዚያም በኋላ ዳዊት ወደ ፋራን ምድረ በዳ ሄደ፤

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

1 ሳሙኤልም ሞተ፥ እስራኤልም ሁሉ ተሰብስበው አለቀሱለት፥ በአርማቴምም በቤቱ ቀበሩት። ዳዊትም ተነሥቶ ወደ ፋራን ምድረ በዳ ወረደ።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ




1 ሳሙኤል 25:1
20 ተሻማሚ ማመሳሰሪያዎች  

በሴ​ይር ተራ​ራ​ዎች ያሉ የኬ​ሬ​ዎስ ሰዎ​ች​ንም በበ​ረሃ አጠ​ገብ እስከ አለ​ችው እስከ ፋራን ዛፍ ድረስ መቱ​አ​ቸው።


በፋ​ራን ምድረ በዳም ተቀ​መጠ፤ እና​ቱም ከም​ድረ ግብፅ ሚስት ወሰ​ደ​ች​ለት።


ሣራም በቈላ ውስጥ ባለች አር​ባቅ በም​ት​ባል ከተማ ሞተች፤ እር​ስ​ዋም በከ​ነ​ዓን ምድር ያለች ኬብ​ሮን ናት፤ አብ​ር​ሃ​ምም ለሣራ ሊያ​ዝ​ን​ላ​ትና ሊያ​ለ​ቅ​ስ​ላት ተነሣ።


በዚ​ያች ምድር የሚ​ኖሩ የከ​ነ​ዓን ሰዎ​ችም በአ​ጣድ አው​ድማ የሆ​ነ​ውን ልቅሶ በአዩ ጊዜ፥ “የግ​ብፅ ልቅሶ እን​ዲህ ታላቅ ነውን?” አሉ፤ ስለ​ዚ​ህም የዚ​ያን ቦታ ስም “ላሐ ግብፅ” ብለው ጠሩት፤ እር​ሱም በዮ​ር​ዳ​ኖስ ማዶ ነው።


የዮ​ዳ​ሄም ልጅ በን​ያስ ወጥቶ ያዘው፤ ገደ​ለ​ውም፤ በም​ድረ በዳም ባለው በራሱ ቤት ቀበ​ረው።


ምና​ሴም ከአ​ባ​ቶቹ ጋር አን​ቀ​ላፋ፥ በቤ​ቱም አጠ​ገብ ባለው በዖዛ አት​ክ​ልት ቦታ ተቀ​በረ፤ ልጁም አሞጽ በእ​ርሱ ፋንታ ነገሠ።


ቍጥሩ ከባ​ሕር አሸዋ የሚ​በ​ልጥ በደ​ልን በድ​ያ​ለ​ሁና፥ ኀጢ​አ​ቴም ብዙ ነውና፤ ከበ​ደ​ሌም ብዛት የተ​ነሣ ቀና ብዬ የሰ​ማ​ይን ርዝ​መት አይ ዘንድ አገ​ባቤ አይ​ደ​ለም። ሰው​ነ​ቴን ከኀ​ጢ​አቴ አሳ​ር​ፋት ዘንድ በብ​ረት ቀፎ ደከ​ምሁ፤ በዚ​ህም ደግሞ አላ​ረ​ፍ​ሁም፤ መዓ​ት​ህን አነ​ሣ​ሥ​ቻ​ለ​ሁና፥


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይጠ​ብ​ቅህ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በቀኝ እጁ ይጋ​ር​ድህ።


“የአ​ሕ​ዛብ ነገ​ሥ​ታት ሁሉ በየ​ቤ​ታ​ቸው በክ​ብር አን​ቀ​ላ​ፍ​ተ​ዋል።


አባቶቻችሁ ወዴት ናቸው? ነቢያትስ ለዘላለም በሕይወት ይኖራሉን?


የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ከሲና ምድረ በዳ በየ​ጉ​ዞ​አ​ቸው ተጓዙ፤ ደመ​ና​ውም በፋ​ራን ምድረ በዳ ቆመ።


ከዚ​ያም በኋላ ሕዝቡ ከአ​ሴ​ሮት ተጓዙ፤ በፋ​ራ​ንም ምድረ በዳ ሰፈሩ።


ገሥ​ግ​ሠ​ውም በቃ​ዴስ ፋራን ምድረ በዳ ወዳ​ሉት ወደ ሙሴና ወደ አሮን፥ ወደ እስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ማኅ​በር ሁሉ ደረሱ፤ ወሬ​ው​ንም ለእ​ነ​ር​ሱና ለማ​ኅ​በሩ ሁሉ ነገ​ሩ​አ​ቸው፤ የም​ድ​ሪ​ቱ​ንም ፍሬ አሳ​ዩ​አ​ቸው።


ሙሴም እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ትእ​ዛዝ ከፋ​ራን ምድረ በዳ ላካ​ቸው፤ እነ​ር​ሱም ሁሉ የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች አለ​ቆች ነበሩ።


ማኅ​በ​ሩም ሁሉ አሮን እንደ ሞተ ባዩ ጊዜ፥ የእ​ስ​ራ​ኤል ቤት ሁሉ ለአ​ሮን ሠላሳ ቀን አለ​ቀሱ።


እስ​ጢ​ፋ​ኖ​ስ​ንም ደጋግ ሰዎች አን​ሥ​ተው ቀበ​ሩት፤ ታላቅ ልቅ​ሶም አለ​ቀ​ሱ​ለት።


የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች በዮ​ር​ዳ​ኖስ በኢ​ያ​ሪኮ አቅ​ራ​ቢያ በሞ​ዓብ ሜዳ ሠላሳ ቀን ለሙሴ አለ​ቀ​ሱ​ለት፤ ለሙ​ሴም ያለ​ቀ​ሱ​ለት የል​ቅ​ሶው ወራት ተፈ​ጸመ።


ማል​ደ​ውም ተነ​ሥ​ተው ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰግ​ደው ሄዱ፤ ወደ ቤታ​ቸ​ውም ወደ አር​ማ​ቴም ደረሱ፤ ሕል​ቃ​ናም ሚስ​ቱን ሐናን ዐወ​ቃት፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አሰ​ባት፤ ፀነ​ሰ​ችም።


ሳሙ​ኤል ግን ሞቶ ነበር፤ እስ​ራ​ኤ​ልም ሁሉ አል​ቅ​ሰ​ው​ለት ነበር፤ በከ​ተ​ማ​ውም በአ​ር​ማ​ቴም ቀብ​ረ​ውት ነበር። ሳኦ​ልም መና​ፍ​ስት ጠሪ​ዎ​ች​ንና ጠን​ቋ​ዮ​ችን ከም​ድር አጥ​ፍቶ ነበር።


ቤቱም በዚያ ነበ​ረና ወደ አር​ማ​ቴም ይመ​ለስ ነበር፤ በዚ​ያም በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ ይፈ​ርድ ነበር፤ በዚ​ያም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊያ ሠራ።


ተከተሉን:

ማስታወቂያዎች


ማስታወቂያዎች