135 በባርያህ ላይ ፊትህን አብራ፥ ሥርዓትህንም አስተምረኝ።
135 በባሪያህ ላይ ፊትህን አብራ፤ ሥርዐትህንም አስተምረኝ።
135 የፊትህን ብርሃን ለባሪያህ አብራለት፤ ሕግህንም አስተምረኝ።
የጽድቅን መሥዋዕት ሠዉ፥ በጌታም ታመኑ።
በዚያን ጊዜም መጻሕፍትን እንዲያስተውሉ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤
ከአንተም አንራቅ፥ አድነን ስምህንም እንጠራለን።
ለጎረቤቶቻችን መከራከርያ አደረግኸን፥ ጠላቶቻችንም ይሣለቁብናል።
በኤፍሬምና በብንያም በምናሴም ኃይልህን አንሣ እኛንም ለማዳን ና።
እነሆ፥ እግዚአብሔር በኃይሉ ልዑል ነው፥ እንደ እርሱስ ያለ አስተማሪ ማን ነው?
መንገዶቼን ዘረዘርሁ፥ ሰማኸኝም፥ ደንቦችህን አስተምረኝ።
አቤቱ፥ አንተ ቡሩክ ነህ፥ ደንቦችህን አስተምረኝ።
ለመዘምራን አለቃ፥ በመለከቶች፥ ስለ አሦራውያን፥ የአሳፍ የምስክር መዝሙር።
የማላየውን ነገር አንተ አስተምረኝ፥ ኃጢአትንም ሠርቼ እንደሆነ፥ ደግሜ አልሠራም የሚለው ማን ነው?
ወደ እግዚአብሔር ይጸልያል፥ እርሱም ይሰማዋል፥ ፊቱንም በደስታ ያሳየዋል፥ ለሰውም የጽድቁን ዋጋ ይመልስለታል።