ምሳሌ 23:31 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)31 ወደ ወይን ጠጅ አትመልከት ሲቀላ፥ መልኩም በብርጭቆ ሲያንጸባርቅ፥ እየጣፈጠም ሲገባ። ምዕራፉን ተመልከትአዲሱ መደበኛ ትርጒም31 መልኩ ቀይ ሆኖ፣ በብርጭቆ ውስጥ ሲያንጸባርቅ፣ ሰተት ብሎ በሚወርድበትም ጊዜ፣ ወደ ወይን ጠጅ ትክ ብለህ አትመልከት። ምዕራፉን ተመልከትአማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም31 ስለዚህ ምንም እንኳ መልኩ በጣም ቀይ ሆኖ በብርጭቆ ውስጥ ቢያንጸባርቅ ሲጠጡትም ሰተት ብሎ ቢገባ የወይን ጠጅ አያስጐምጅህ። ምዕራፉን ተመልከትየአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)31 ወደ ጽዋዎችና ወደ ብርሌ ዐይንህን ብትሰጥ፥ በኋላ እንደ ግንብ ዕራቁትህን ትሄዳለህ፤ ምዕራፉን ተመልከት |