ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ መጽሐፈ ዮዲት 12:16 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)16 ዮዲትም ገብታ ተቀመጠች፤ የሆሎፎርኒስ ልብ ተደነቀች፤ ከእርሷም ጋር ለመተኛት ነፍሱ ፈጽማ ታወከች፤ እርሷን ካየበት ቀን ጀምሮ እርሷን ለማሳሳት ምቹ ጊዜ ይፈልግ ነበር፤ ምዕራፉን ተመልከትየአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)16 ዮዲትም ወደ እርሱ ገብታ ተቀመጠች፤ የሆሎፎርኒስም ልቡናው በእርሷ ታወከ፤ ከእርሷም ጋር ይተኛ ዘንድ ሰውነቱ ፈጽማ ጐመጀች፤ ከአያትም ጀምሮ እርሷን እስከሚያባብልበት ጊዜ ይጠብቃት ነበር። ምዕራፉን ተመልከት |